top of page

ህዳር 7፣2016 - ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታን በአዋሽ ባንክ በኩል ከሁሉም ቦንኮች መክፍል የሚያስችል ስምምነት ተደረገ።

  • Nov 17, 2023
  • 1 min read

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራሁ ተሊላ እና የአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራሁ ተፈራርመዋል።


በስመምነቱ መሰረት ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያን በሀገሪቱ ያሉ ሁሉም ባንኮች ያላቸውን የከፍያ ሥርዓት አዋሽ ባንክ ካሰናዳው የመክፈያ ስርዓት ጋር በማስተሳሰር ደንበኞች ክፍያ እንዲፈጽሙ የሚያስችል ነው ተብሏል።


የመክፈያ ስርዓቱ መጀመር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሁሉም የፋይናንስ ተቋማት ጋር ሲስተሙን ማስተሳሰር ሳይጠበቅበት፣ በቀጥታ ከአዋሽ ባንክ ሲስተም ጋር እንዲያስተሳሰሩ በማድረግ፣ ለሲስተም ማስተሳሰር የሚያወጣዉን ክፍተኛ ወጪ ያስቀርለታል ሲሉ የአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራሁ ተናግረዋል ።


የአዋሽ ባንክ ደንበኞች በባንኩ ቅርንጫፎች፣ በአዋሽ ብር-ፕሮ የሞባይል ባንኪንግ መተግበርያ አማካይነት የኤሌክትሪክ ፍጆታቸውን መክፈል ይችላሉ ሲሉ ስራ አስፈጻሚው አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከአዋሽ ባንክ ጋር ያደረኩት ስምምነት የደንበኞቼን የአገልግሎት እርካታ ለመጨመር የሚሰራ ስራ አካል ነው ብሏል።


የአገልግሎቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራሁ ተሊላ አገልግሎቱ በንግድ ባንክ እና በቴሌ ብር አማካይነት የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያ እንደሚቀበል አስታውሰዋል።


ይሁን እንጂ የመክፈያ ስርዓቱ በዚህ በመወሰኑ ደንበኞች ቅሬታ ሲያቀርቡ እንደነበር ተናግረዋል።


በዚህም መሰረት ስርዓቱን መዘርጋት ማስፈለጉን ጠቅሰዋል።


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 5 ሚሊዮን ደንበኞች አሉኝ ያለ ሲሆን ደንበኞቼ የፍጆታ ክፍያቸውን በአሻቸው የክፍያ አማራጭ እንዲከፍሉ አማራጩን እያስፋፋሁ እሄዳለሁ ብሏል።





የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
ከአምስት አመት በኋላ በምግብ እጥረት ምክንያት የሚቀነጭሩ ህጻናት እንዳይኖሩ በሰቆጣ ቃል ኪዳን የገባችው ኢትዮጵያ እስካሁን በከወነችው ስራ ምን ውጤት አገኘች?

ሰኔ 15/2018 ከአምስት አመት በኋላ በምግብ እጥረት ምክንያት የሚቀነጭሩ ህጻናት እንዳይኖሩ በሰቆጣ ቃል ኪዳን የገባችው ኢትዮጵያ እስካሁን በከወነችው ስራ ምን ውጤት አገኘች? በ2025 ስራውን በ700 ወረዳዎች ላይ ተግባራዊ አደርጋለሁ ብትልም እዛ ማድረስ ግን አልቻለችም ታዲያ ከ አምስት አመት በኋላ እንደቃሏ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page