በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ።
- 28 minutes ago
- 1 min read
ነሐሴ 7 2018
በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ።
ከአስር ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የታየው የኤልኒኖ ተፅዕኖ የእህል ምርት ውጤትን ከ15 እስከ 20 በመቶ እንዲቀንስ አድርጎ እንደነበር አንድ የዘርፉ ተመራማሪ ነግረውናል።
ክስተቱ ከፍቶ በታየባቸው የኢትዮጵያ ምስራቃዊ አካባቢዎች የእህል ምርት ቅናሹ ከ40 በመቶ በላይ እንደነበር በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰርና በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ተባባሪ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ሠለሞን ዜና ያስታወሱት።
ተፅዕኖው ምግብ እና ለስላሳ መጠጥ አምራች ፋብሪካዎች ላይም መታየቱን ዶክተር ሠለሞን ተናግረዋል።
የእነዚህ ፋብሪካዎች ምርታማነት በ25 በመቶ ቀንሷል ያሉ ሲሆን ሽያጫቸውም በ39 በመቶ ዝቅ ማለቱን ጠቅሰዋል።
የፋብሪካዎቹ ምርታማነትም በ26 በመቶ ቀንሶ ታይቷል ብለዋል።
ዘንድሮም በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይ የኤልኒኖ ተፅዕኖ ይታያል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.....
ንጋቱ ረጋሣ
_edited.jpg)


Comments