top of page

ህዳር 29፣ 2015የፔሩ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው የቆዩት የ60 ዓመቷ ዲና ቦሉአርቴ የአገሪቱ ተጠባቂ ፕሬዝዳንት በመሆን ቃለ መሐላ ፈፀሙ፡፡

  • Dec 8, 2022
  • 1 min read

ህዳር 29፣ 2015


የፔሩ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው የቆዩት የ60 ዓመቷ ዲና ቦሉአርቴ የአገሪቱ ተጠባቂ ፕሬዝዳንት በመሆን ቃለ መሐላ ፈፀሙ፡፡


ፕሬዝዳንት የነበሩት ፔድሮ ካስቲሎ በፓርላማው ተከስሰው ከስልጣን ከተወገዱ በኋላ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ TRT ዎርልድ ፅፏል፡፡


አጋጣሚው ድራማዊ ሁኔታ አላጣውም ተብሏል፡፡


ፔድሮ ካስቲሎ ተከስሰው ከስልጣን ከመወገዳቸው አስቀድሞ በቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት ፓርላማውን በትኘዋለሁ ብለው እንደነበር ተሰምቷል፡፡


ካስቲሎ በፓርላማው ተከስሰው ከስልጣን

መወገዳቸው ተከትሎ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው የቆዩት ዲና ቦሉአርቴ ወዲያውኑ ቃለ መሐላ በመፈፀም የአገሪቱ የመጀመሪያዋ ሴት ጊዜያዊ ርዕሰ ብሔር መሆናቸው ታውቋል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Recent Posts

See All
የሐምሌ 17 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ብሪታንያ የብሪታንያ መንግስት በኬንያ ላካሂድ የነበረውን አመታዊ የጦር ልምምድን ትቼዋለሁ አለ፡፡ የብሪታንያ ሰራዊት አመታዊ የኬንያ የጦር ልምምዱን የተወው ከምስራቅ አፍሪካዊቱ አገር መንግስት ፈቃድ ባለማግኘቱ ነው መባሉን አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ የብሪታንያ ጦር ከዚህ ቀደም በኬንያ በየአመቱ በመደበኛነት የጦር ልም

 
 
 
የሐምሌ 16 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሊቢያ በሊቢያ የተለያዩ የፖለቲካ ማህበራት አገሪቱ ወደ አንድነቷ እንድትመለስ ጥሪ አቀረቡ፡፡ የፖለቲካ ማህበራቱ በጋራ የህውደት ጥሪውን ያቀረቡት የሊቢያን የወደፊት እጣ ፈንታ በተመለከተ ምክክር ባደረጉበት ወቅት እንደሆነ TRT አፍሪካ ፅፏል፡፡ በሊቢያ የቀድሞው መሪ የኮሎኔል ሙአመር ጋዳፊ አስተዳደር ከ15 አመታት

 
 
 
የሐምሌ 15 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሞሪታንያ በሞሪታንያ የባህር ዳርቻ አቅራቢያ በደረሰ የባህር አደጋ 144 ጥገኝነት ፈላጊዎቹ ሳይሞቱ አልቀረም ተባለ፡፡ የአደጋው ሟቾች መነሻዋን ከጋምቢያ በማድረግ ወደ ስፔን በማምራት ላይ በነበረች ጀልባ የተሳፈሩ ጥገኝነት ፈላጊዎች እንደሆኑ አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ በጀልባዋ ተሳፍረው የነበሩት በሙሉ ከተለያዩ የአፍ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page