top of page

ህዳር 27፣ 2015- የኢንዶኔዥያ ፓርላማ ከጋብቻ ውጭ የሚደረግን ወሲባዊ ግንኙነት የሚነውር ህግ አፀደቀ፡፡

ህዳር 27፣ 2015


የኢንዶኔዥያ ፓርላማ ከጋብቻ ውጭ የሚደረግን ወሲባዊ ግንኙነት የሚያነውር ህግ አፀደቀ፡፡


ሕጉ ከጋብቻ ውጭ ወሲብ የሚፈፅሙት በ1 ዓመት እስር እንዲቀጡ የሚጠይቅ እንደሆነ ኢቭኒንግ ስታንዳርድ ፅፏል፡፡


የሕጉ የተፈፃሚነት ወሰን ወደ ኢንዶኔዥያ የሚገቡ አገር ጎብኚ ቱሪስቶችንም ይመለከታል ተብሏል፡፡


ሕጉ አሁን ቢፀድቅም ተፈፃሚነቱ እንደሚዘገይ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


ሕጉን ሥራ ላይ ማዋሉ በጥቂቱ የአመት ጊዜ ሊጠይቅ ይችላል ተብሏል፡፡


የሕጉ ሥራ ላይ መዋያ የሚዘገየው የማስፈፀሚያ ደንብ እና መመሪያዎችን ለማሰናዳት ሲባል መሆኑ ታውቋል፡፡


የኔነህ ከበደ



ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page