በፊንቴክ የማጭበርበር ወንጀል ዛሬ በአቃቤ ሕግ ክስ የተመሰረተባቸው አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ተወነሰ፡፡
- 2 hours ago
- 1 min read
ሚያዝያ 28/2018
በፊንቴክ የማጭበርበር ወንጀል ዛሬ በአቃቤ ሕግ ክስ የተመሰረተባቸው አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ተወነሰ፡፡
በተጠርጣሪዎቹ ላይ በአቃቤ ህግ ዛሬ የመሰረተባቸውን የክስ ዝርዝሩን ያደመጠው የከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ከአምስተኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማል በስተቀር ሌሎቹ በዋስ እንዲፈቱ ወስኗል፡፡
አቃቤ ህግ መንሱር ጀማልን በዋስትና እንዳይፈታ በመቃወሙ፣ መቃወሚያውን በፅሁፍ እንዲያስረዳ ችሎቱ ለመጪው ሰኞ ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በዋስ እንዲለቀቁ ለተወሰነላቸው ተከሳሾችም በዋስትና የሚለቀቁበትን የገንዘብ መጠን ለመወሰን ፍርድ ቤቱ ለመጪው ሰኞ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ተከሳሾች የ 1.9 ቢሊን ብር የማጭበርበር ጉዳት አድርሰዋል ያለው አቃቤ ሕግ ከደረሰው ጉዳት አንፃር የዋስትና ብሩ ከፍ እንዲልለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡
በተጨማሪም ተከሳሾቹ የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ከእሰር ቢለቀቁ እንኳን ከሀገር እንዳይወጡ እገዳ እንዲጣልለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡
አቃቤ ህግ ዛሬ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው የክስ ዝርዝር ዳንኤል ዩሃንስ ከተባለው ተከሳሽ እና ለጊዜው ካልተያዙ ተጠርጣሪዎች ጋር በመሆን የኮምፒውተር ስርዓትን በመጠቀም አሳሳች መረጃን በማሰራጨት መግለፅ የሚገባቸውን መረጃ በመደበቅ የሶስተኛ ወገን ጥቅምን የሚጎዳ ድርጊት እንዲፈፀም ለማድረግ በማሰብ ስምምነት ማድረጋቸው ተጠቅሷል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments