ኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤ ልታሰናዳ ነው፡፡
- 1 hour ago
- 1 min read
ሚያዝያ 28/2018
ኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤ ልታሰናዳ ነው፡፡
ጉባኤው ለተማሪዎች ምገባ እና የትምህርት ቁስ ድጋፍ ለሚከነው ስራ የሚታዩ የፋይናንስ ችግሮችን ለመፍታት ያግዛል ተብሏል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተቋቋመው የቀዳማይ ልጅነት ማዕከል የልጆችን የተሟላ የጤና እንክብካቤ፣ የተመጣጠነ ምግብ እና ጥራት ያለው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት መከታተል ዋና አላማው እንደሆነም ሰምተናል።
በዚህም 241 የመንግስት ትምህርት ቤቶች እና በ935 የቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤቶች ላይ የምገባ ፕሮግራም፣ የትምህርት ቁሳቁስ በማቅረብ እና የተማሪዎች ዩኒፎርም በነፃ በማቅረብ አገልግሎት እየሰጠ እንደሆነም እና ከ330,000 በላይ ተማሪዎች የዚሁ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸው የቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል ዋና ስራ አስፈፃሚ ከበደ ወርቁ(ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

በዚህም ኢትዮጵያ ከግንቦት 3 እስከ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በምታካሔደው ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤ ከሌሎች የአለም ሃገራት ጋር ትመካከራለች ተብሏል፡፡
ጉባኤው አፍሪካ በቀዳማዊ ልጅነት ሥርዓት ለውጥ የግንባር-ቀደምትነት ሚና ከአካባቢያዊ ሞዴሎች ወደ ዓለም አቀፍ እንቅስቃሴ በሚል ይካሄዳል ተብሏል።
በጉባኤው ከሀገር ውስጥ፣ ከአፍሪካ፣ ከሌሎች የዓለም ሃገራት የተወጣጡ ከ350 በላይ ተሳታፊዎች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ ጉባኤ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት የሚያግዝ የውይይት፣ የልምድና ዕውቀት ልውውጥእንዲሁም የመማማሪያ መድረክ ከመሆኑ ባሻገር የመፍትሄ ሀሳቦች እንደሚቀርቡበት ይጠበቃል ተብሏል።
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7




Comments