top of page

ኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤ ልታሰናዳ ነው፡፡

  • 1 hour ago
  • 1 min read

ሚያዝያ 28/2018


ኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤ ልታሰናዳ ነው፡፡


ጉባኤው ለተማሪዎች ምገባ እና የትምህርት ቁስ ድጋፍ ለሚከነው ስራ የሚታዩ የፋይናንስ ችግሮችን ለመፍታት ያግዛል ተብሏል፡፡


በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተቋቋመው የቀዳማይ ልጅነት ማዕከል የልጆችን የተሟላ የጤና እንክብካቤ፣ የተመጣጠነ ምግብ እና ጥራት ያለው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት መከታተል ዋና አላማው እንደሆነም ሰምተናል።


በዚህም 241 የመንግስት ትምህርት ቤቶች እና በ935 የቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤቶች ላይ የምገባ ፕሮግራም፣ የትምህርት ቁሳቁስ በማቅረብ እና የተማሪዎች ዩኒፎርም በነፃ በማቅረብ አገልግሎት እየሰጠ እንደሆነም እና ከ330,000 በላይ ተማሪዎች የዚሁ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸው የቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል ዋና ስራ አስፈፃሚ ከበደ ወርቁ(ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡



በዚህም ኢትዮጵያ ከግንቦት 3 እስከ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በምታካሔደው ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤ ከሌሎች የአለም ሃገራት ጋር ትመካከራለች ተብሏል፡፡


ጉባኤው አፍሪካ በቀዳማዊ ልጅነት ሥርዓት ለውጥ የግንባር-ቀደምትነት ሚና ከአካባቢያዊ ሞዴሎች ወደ ዓለም አቀፍ እንቅስቃሴ በሚል ይካሄዳል ተብሏል።


በጉባኤው ከሀገር ውስጥ፣ ከአፍሪካ፣ ከሌሎች የዓለም ሃገራት የተወጣጡ ከ350 በላይ ተሳታፊዎች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል።


ይህ ጉባኤ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት የሚያግዝ የውይይት፣ የልምድና ዕውቀት ልውውጥእንዲሁም የመማማሪያ መድረክ ከመሆኑ ባሻገር የመፍትሄ ሀሳቦች እንደሚቀርቡበት ይጠበቃል ተብሏል።


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….

ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Recent Posts

See All
በፊንቴክ የማጭበርበር ወንጀል ዛሬ በአቃቤ ሕግ ክስ የተመሰረተባቸው አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ተወነሰ፡፡

ሚያዝያ 28/2018 በፊንቴክ የማጭበርበር ወንጀል ዛሬ በአቃቤ ሕግ ክስ የተመሰረተባቸው አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ተወነሰ፡፡ በተጠርጣሪዎቹ ላይ በአቃቤ ህግ ዛሬ የመሰረተባቸውን የክስ ዝርዝሩን ያደመጠው የከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ከአምስተኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማል በስተቀር

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page