top of page

ሁለተኛው ግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ፕሮጀክት በነገው ዕለት ይፋ እንደሚደረግ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ተናገረ

  • sheger1021fm
  • 1 hour ago
  • 1 min read

ህዳር 8 2018

 

ሁለተኛው ግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ፕሮጀክት በነገው ዕለት ይፋ እንደሚደረግ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡

 

ስራውን ለመተግበርም 128 ሚልዮን ዶላር ያስፈልጋል ተባለ፡፡

 

የመጀመሪያው የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ስራ ላለፉት 6 ዓመት ሲተገበር ነበር የተባለ ሲሆን 102 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ተደርጎበታል ተብሏል፡፡

 

በ2012 ዓ.ም በ600,000 ሄክታር መሬት ወደ ስራ ያስገባው የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር 4.4 ሚልየን ገበሬ በክላስተር ተደራጅቶ የቴክኖሎጂና የተሻለ ግብዓት ተጠቃሚ ለማድረግ እንደተሰራ ሰምተናል፡፡

 

ባለፉት 6 ዓመታት በተሰራው ስራ 12 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በክላስተር እየታረሰ ነው ያሉት በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ዋና ዳይሬክተሩ ዳኛቸው ሌሉ(ዶ/ር) ናቸው፡፡

 

ከዚህ ባለፈም በክላስተር ሲታረስ ምርት ለመሰብሰብ የተሻሉ ቴክኖሎጂዎችን ለመጠቀም እና የምርት ብክነትን ለማስቀረት ይረዳል ሲሉም ጠቅሰዋል፡፡

 

የ2ኛ ዙር የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ግብርና ስራ 6.5 ሚሊዮን ገበሬን ተጠቃሚ ለማድረግ እቅድ ተይዟል ብለዋል፡፡

 

ከያዝነው 2018 እስከ 2022 ድረስ ይተገበራል ለተባለው 2ተኛው ምዕራፍ 128 ሚሊየን ዶላር ለስራው ያስፈልጋል ተብሏል፡፡

 

እስካሁንም ድረስ ከረጂ ተቋማት 66 ከመቶ የሚሆነው በጀት ተገኝቷል፡፡

 

ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….

 በረከት አካሉ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇

 

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page