top of page
  • sheger1021fm

ታህሳስ 8፣ 2015- ፀሐይ ባንክ ካፒታሉን ወደ 5 ቢሊየን ብር ለማሳደግ ዛሬ በአንደኛው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ መወሰኑ ተሰማ


ፀሐይ ባንክ ካፒታሉን ወደ 5 ቢሊየን ብር ለማሳደግ ዛሬ በአንደኛው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ መወሰኑ ተሰማ፡፡


የባንኩ ካፒታል 2 ቢሊየን 162 ሚሊየን 534 ሺህ ብር በመጀመር ወደ 5 ቢሊየን ብር እንዲያድግ ተወስኗል፡፡


ይህም የገንዘብ መጠን እንደ ጎርጎሮሳዊው አቆጣጠር 2024 ድረስ ተከፍሎ ይጠናቀቃል ተብሏል፡፡


በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት ባንኮች ሊኖራቸው የሚገባው ዝቅተኛ የካፒታል መጠን ላይ ማሻሻያ በመደረጉ እና ይሄንኑ ማሻሻያ በተገቢው መልኩ ማሟላት አስፈላጊ ነው ብሏል፡፡


የፀሐይ ባንክ ካፒታል አቅሙን በመጨመር ከሌሎች ባንኮች ጋርም ተወዳዳሪ ለማድረግ እንዲቻል እየተሰራ ነው ተብሏል፡፡


የውጪ ባንኮች በአገር ቤት ገብተው እንዲሰሩ የሚፈቀድ ፖሊሲ በመውጣቱ በባንኮች ላይ በሚፈጠረው ውድድር አሸናፊ ሆኖ ለመውጣት ፀሐይ ባንክ የተሻለ የካፒታል ቁመና ላይ መገኘት አስፈላጊ ነው ብሏል፡፡


ፀሐይ ባንክ የተፈረመ ካፒታል 2 ቢሊየን 837 ሚሊየን 466 ሺህ ብር ነው፡፡


የተከፈለ ካፒታሉ ደግሞ 865 ሚሊየን 976,500 ብር ነው፡፡


ተህቦ ንጉሴ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All

በኢትዮጵያ የካፒታል ወይም ድርሻዎች ገበያ መሳተፍ ለሚፈልጉ ተቋማት ከ3 እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ፍቃድ መስጠት ይጀመራል ተባለ። ፍቃድ የሚሰጣቸውን ተቋማት ለመለየት መመሪያ መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ የተመለከተ ምክክር

በጋሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ የዘይሴ እና የቁጫ ብሔረሰቦች ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው ነው ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑ እንደራሴዎች ተናገሩ፡፡ ለሚደርሰው በደል ዋነኛው ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች በምርጫ ወቅት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን በመምረጣቸው ነው ብለዋል፡፡ ንጋቱ ሙሉ ሸገርን ወሬዎች፣ መ

በአፋርና በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት የወደሙ ት/ቤት መልሶ መገንቢያ እስካሁን 2.8 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል ተባለ፡፡ በጦርነቱ ከ300 ት/ቤቶች በላይ ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ይታወሳል፡፡ ተመስገን አባተ ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page