ተማሪዎች የሰው ሠራሽ አስተውህሎት (AI) አጠቃቀም ላይ ከመምህራኖቻቸው ቀድመው የሚገኙ ከሆነ በመማር ማስተማር ሂደት ላይ ክፍተት መፍጠሩ አንደማይቀር ተጠቆመ።
- 3 hours ago
- 1 min read
ነሐሴ 12 2018
ተማሪዎች የሰው ሠራሽ አስተውህሎት (AI) አጠቃቀም ላይ ከመምህራኖቻቸው ቀድመው የሚገኙ ከሆነ በመማር ማስተማር ሂደት ላይ ክፍተት መፍጠሩ አንደማይቀር ተጠቆመ።
ችግሩን ለመቅረፍ መምህራንን በቴክኖሎጂው ማብቃትና AIን በራሱ እንደ አንድ የትምህርት ኮርስ አዋህዶ መስጠት እንደሚያስፈልግ የዘርፉ ተመራማሪዎች አሳስበዋል።
ሰው ሰራሽ አስተውህሎት እያሳየ ባለው እድገት ምክንያት ከጊዜ በኋላ መምህራንን ሊተካ ይችላል የሚል ስጋትን ደቅኗል ተባለ፡፡
በኮተቤ የትምህርት ዩንቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር አበበ አለሙ መምህራኑ በአግባቡ ለዚህ ቴክኖሎጂ ማዘጋጀት ከተቻለ ጊዜያቸውን እንዲጠቀሙ ተማሪዎቻቸውንም እንዲያበቁ ይረዳቸዋል ይላሉ፡፡
ይህ ካልሆነ ግን ቴክኖሎጂው እየሄደበት ባለው ፍጥነት ያልበቃውን መምህር ሊተካ ይችላል ፣ ተማሪዎችም መምህሩን እንዲበልጡት ሊያደርግ ይችላል ሲሉም ስጋታቸውን ነግረውናል፡፡
ሌላኛዋ በሰው ሰራስ አስተውህሎት ዘርፍ ተመራማሪ የሆኑት ሰርካለም ንጉሴ ሰው ሰራሽ አስተውህሎት ጥቅም ላይ ሲውል ጥንቃቄን ይፈልጋል ብለዋል፡፡
ተማሪዎች ከዚህ ቴክኖሎጂ ጋር ያላቸው ቅርበት ከመምህራኑ የቀደመ ሆኖ ይገኛል ያሉት ተመራማሪዋ መምህራን ስልጠና ሲሰጣቸው ይህን ቴክኖሎጂ እንዴት ረዳት አድርገው እንደሚጠቀሙት ማስተማር ይገባልም ሲሉ አስረድተዋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ....
በረከት አካሉ
_edited.jpg)



Comments