የክልሎች ህገ መንግስት በክልሉ ያሉ ሁሉንም ብሔሮችን በሚጠብቅ መልኩ እንዲሻሻል እና "ልዩ ሃይል" አፍርሰናል ያሉ ክልሎች በገለልተኛ አካል ኦዲት እንዲደረጉ በተቋማት ግንባታ ስር ሲመክር የቆየው ቡድን ያለ ልዩነት መስማማቱ ተነገረ።
- 1 hour ago
- 2 min read
ነሐሴ 13 2018
የክልሎች ህገ መንግስት በክልሉ ያሉ ሁሉንም ብሔሮችን በሚጠብቅ መልኩ እንዲሻሻል እና "ልዩ ሃይል" አፍርሰናል ያሉ ክልሎች በገለልተኛ አካል ኦዲት እንዲደረጉ በተቋማት ግንባታ ስር ሲመክር የቆየው ቡድን ያለ ልዩነት መስማማቱ ተነገረ።
በተቋማት ግንባታ ስር ሲመክር የቆየው ቡድን "ልዩ ሃይል" አንዲፈርስ ፣የክልል ፖሊስም በአገር አቀፍ ደረጃ ወጥ ሆኖ በሚዘጋጅ የስልጣን ሰነድ እንዲሰለጥን ከስምምነት መድረሳቸውን ሸገር ከቡድኑ አባላት ሰምቷል።
ክልሎች የሚኖሯቸው የሚሊሻ አባላትም በወታደራዊ ሳይንስ የሰለጠኑ ይሁኑ በሚለው መመሪያ ላይ የተስማማው ቡድኑ አንድም የክልል የጸጥታ አደረጃጀት የመከላከያ እና ፌደራል ፖሊስን የሚገዳደር ሃይል እንዳይኖረው በሚለው መስማማታቸውን ተመካካሪዎች ነግረውናል ።
ተመካካሪው ብድን ክልሎች አፍርሰናል ያሉት "ልዩ ሃይል " በገልተኛ ወገን ኦዲት እንዲደረግ ተስማምተናል ብለዋል።
ተመካካሪዎች ገለልተኛ ቡደን የተባለው አካል ሲጠቅሱ ደግሞ መከላከያ እና የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን ለማሳየት ዘርዝረዋል ።
ሌላው ይህ ቡድን መከርኩበት እና ተስማማሁበት ያለው በክልሎች ለንጽሃን መፈናቅል "ምክንያት "ናቸው ያላቸውን የክልሎች ህገ መንግስትን የተመለከተ ነው።
በዚህ የአንዳንድ ክልሎች ህገመንግስት ዜጎች ያለ ክልላቸው ሃብት ጥበቃ አይደርግም ይህም ለንጽሁን መፈናቅል ምክንያት ሆኗል ።
ሰለዚህ ለክልሉ ብሔሮች ብቻ ሃብት እንዲፈሩ የሚፍቅዱ የክልል ህገ መንግስቶች እንዲሻሻሉ ተጠይቋል።
አንዚህ ምክረ ሀሳቦች የመጨረሻ ለመሆነ ነገ በጉባዔተኞች መጽደቅ ይኖርበታል ።
በሌላ በኳል በለፉት ቀናት በተመረጡ 34 አጠናቃሪዎች እርስ በእርስ እንዳይጋጩ ሲጣጣሙ የቆዩ አጀንዳዎች ዛሬ ለ500 ቡድን አባላት ይቀርባሉ።
ቡድንም ተጣጥመው በቀረቡት አጀንዳዎች ላይ የመጨረሻ ግብዓት ሰጥቶ በሳምቱ መጨረሻ 4ሺውም ጉባዔተኛ ለአጀንዳዎች የቀረቡ ምክረ ሀሳቦችን ያጽድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
እስካሁን ባለው ሂደት ለአጀንዳዎች የቀረቡ ወይንም የተሰጡ ምክረ ሀሳቦች በሁሉም ባይሆንም በተወሰኑት ከአንድ በላይ ናቸው።
እንዚህም ምክረ ሀሳቦች ወደ አንደ እንዲጠቡ የምክክር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሂሩት ገብረ ስላሴ ለ4ሺ ተመካካሪዎች ትናንት ነሃሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረጉት ንግግር ጥሪ አቅርበዋል ።

ምክትል ኮሚሽነሯ እዚህ የመጣውን ለመስማማት ስለሆ ምክረ ሀሳቦችን ወደ አንድ ማጥበብ አለብን ብለዋል።
አዲስ አበባ ላይ ሲመክር የቆየው ብድንን ጨምሮ ከፍተኛ ክርክር እና ልዪነት ያለባቸው ምክር ሀሳቦች እንዴት ወደ አንድ ምክረ ሀሳብ ይሰበሰባል የሚለው የሚጠበቅ ይሆናል።
ያሬድ እንዳሻው
_edited.jpg)


Comments