top of page

ትምህርት ሚኒስቴር ባስገነባቸው 9 ልዩ አዳሪ ትምህርትቤቶች ተማሪዎችን ፈትኖ ለመቀበል መዘጋጀቱን የትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ፡፡

  • 1 day ago
  • 1 min read

ነሐሴ 13 2018


ትምህርት ሚኒስቴር ባስገነባቸው 9 ልዩ አዳሪ ትምህርትቤቶች ተማሪዎችን ፈትኖ ለመቀበል መዘጋጀቱን የትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ፡፡



ባለፈው አመት በ5 ልዩ አዳሪ ትምህርትቤቶች 1ሺ 250 ተማሪዎች ተቀብሎ እያስተማረ እንደነበር የጠቀሰው ትምህርት ሚኒስቴር ተጨማሪ 4 ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በመጪው የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን መቀበል ይጀምራሉ ብሏል፡፡


ባህር ዳር ፣ አርባ ምንጭ ፣ ድሬዳዋ እና አሶሳ አዳዲስ ልዩ ኣዳሪ ትምህርትቤቶች ሲሆኑ ቡኢ ፣ ወሊሶ ፣ጅግጅጋ ፣ ጋምቤላ እና ቦንጋ ደግሞ ነባሮቹ የፌደራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ናቸው፡፡


ዘንድሮ ወደ ፌደራል ልዩ አዳሪ ትምህርትቤት ለመወዳደር የ8ተኛ ክፍል ውጤታቸው 80 ከመቶና ከዛ በላይ ያመጡ ተማሪዎች ኬጥኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ለመወዳደር ብቁ ናቸው ተብሏል፡፡


ከጠረፍ እና አርብቶ አደር ከሆኑ አካባቢዎች የሚመጡ ተማሪዎች ካለው ሁኔታ ጋር በተያያዘ ውጤታቸው ዝቅ ቢልም በልዩ ሁኔታ ሊታዩ እንደሚችሉ ተጠቅሷል፡፡


በሁሉም ክልሎች ቢያንስ አንድ ልዩ አዳሪ ትምህርትቤት ለመክፈት ትምህርት ሚኒስቴር እየሰራ ነው ተብሏል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ...


በረከት አካሉ

Recent Posts

See All
ባለፉት ጊዜያት በነበረው የ12ኛ ክፍል የተማሪዎች ውጤት ዝቅ ማለት «ተማሪዎች የመማር ፍላጎታቸው እየቀነሰ ነው» የሚል ሀሳብ ሲነሳ ይደመጣል።

ነሐሴ 14 2018 ባለፉት ጊዜያት በነበረው የ12ኛ ክፍል የተማሪዎች ውጤት ዝቅ ማለት «ተማሪዎች የመማር ፍላጎታቸው እየቀነሰ ነው» የሚል ሀሳብ ሲነሳ ይደመጣል። በሌላ በኩል ደግሞ ይህ የፈተና ስርዓት ጥብቅ መሆኑ ተማሪዎችን የበለጠ በራሳቸው እንዲተማመኑ እያደረገ ነው የሚል ሃሳብ ከሌላኛው ወገን ይነሳል። አሁን በ

 
 
 
በኢትዮጵያ ሥርዓተ ምግብን፣ የአየር ንብረት ለውጥንና ሥርዓተ ጾታን የተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ሥራዎች አንዱ ከአንዱ ጋር ተናበው የሚከወኑ ባለመሆናቸው ውጤት ከማምጣት ይልቅ ችግሩን ውሃ ቅዳ፣ ውሃ መልስ አድርጎታል ተባለ።

ነሐሴ 14 2018 በኢትዮጵያ ሥርዓተ ምግብን፣ የአየር ንብረት ለውጥንና ሥርዓተ ጾታን የተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ሥራዎች አንዱ ከአንዱ ጋር ተናበው የሚከወኑ ባለመሆናቸው ውጤት ከማምጣት ይልቅ ችግሩን ውሃ ቅዳ፣ ውሃ መልስ አድርጎታል ተባለ። ሥርዓተ ምግብና የአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዘው የሚከሰቱት ችግሮች ተጽዕኗ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page