ፖሊስ በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት፡፡
- 13 minutes ago
- 1 min read
ሚያዝያ 14/2018
ፖሊስ በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት፡፡
ፖሊስ ተጨማሪ 14 ቀን ለምርመራ እንዲፈቀድለት ባለፈው አርብ በነበረው ችሎት ጠይቆ ለውሳኔ ፍርድ ቤቱ ለዛሬ ቀጥሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡
በ"ፊንቴክ"(Fintech) ኢንቨስትመንት ሽፋን በተፈጸመ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮችን ጉዳይ ፖሊስ በጠየቀው የተጨማሪ ጊዜ ላይ ለመወሰን የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዛሬ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ለፖሊስ የ7 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።
ባለፈው ሚያዚያ 9 2018 ዓ/ም በነበረው ችሎት ባለፉት ቀናት ያከናወናቸውን ተግባራት ለችሎቱ ያስረዳው ፖሊስ፣ ነገር ግን ከወንጀሉ ውስብስብነትና ስፋት አንፃር ቀሪ የምርመራ ስራዎችን ለማጠናቀቅ ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲሰጠው ጠይቆ ነበር።
በተቃራኒው የተጠርጣሪዎች ጠበቆች ደንበኞቻቸው በህዝብ ዘንድ የሚታወቁና ቋሚ መኖሪያ ያላቸው መሆኑን እና የራሳቸው መተዳደሪያ ስራ ያላቸውና አብዛኞቹም የጤና እክል ያለባቸው ናቸዉ በማለት የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ተከራክረዋል።
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ፣ ውሳኔ ለመስጠት ለዛሬ ሚያዚያ 14 2018 ዓ/ም ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።
ዛሬ በነበረው ችሎት ፖሊስ የቀረውን ምርመራ አጠናቆ እንዲያቀርብ 7 ተጨማሪ ቀናት ፈቅዷል።
ተጠርጣሪዎቹ ለቀጣይ የችሎት ቀጠሮ ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ አዟል።
ገዛ ጌታሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments