ሰኔ 16/2018 - የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ትግበራ ሂደት እስካሁን አለመጀመሩ እንዳሳሰበው ኢሰመኮ ተናገረ፡፡
- 1 hour ago
- 1 min read
ሰኔ 16/2018
የኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ትግበራ ሂደት እስካሁን አለመጀመሩ እነዳሳሰበው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ተናገረ፡፡
ኮሚሽኑ የተዘጋጁት ረቂቅ ሕጎችና ሰነዶችም ለሕዝብ ውይይት እስከ አሁን አለመቅረባቸው ያሳስበኛል ብለዋል።
ኮሚሽኑ ይህን የተናገረው ዛሬ ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም የ11 ወራት አቅድ አፈጻጸሙን ሪፖርት ለህዘብ እንደራሴዎች ምክርቤት ባቀረበበት ሰነዱ ላይ ነው፡፡
በሚያዝያ 2016 ዓ.ም የጸደቀው የኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ትግበራ ፍኖተ ካርታ በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም ይፋ መደረጉን ያስታወሰው ኮሚሽኑ በሽግግር ፍትሕ ፖሊሲው የተመላከቱትን ዋና ዋና ተቋማት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጆች መቀረጻቸው ጠቅሰዋል፡፡

ፖሊሲውን ለማስፈጸም መሰረት የሆነው የዓለም አቀፍ ወንጀሎች ሕግ ከሽግግር ፍትሕ ሂደት መጠናቀቅ በኋላም በዘላቂነት ተግባራዊ ሊደረግ በሚችልበት አግባብ መረቀቁ ተገቢ መሆኑን አስረድቷል፡፡
በሽግግር ፍትሕ ሂደት የተጎጂዎችንና ለሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ተጋላጭ የሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ተሳትፎ የሚመራ ረቂቅ ስትራቴጂ በመዘጋጀት ላይ መሆኑን አክሏል፡፡
ይሁንና በሽግግር ፍትሕ ትግበራ ፍኖተ ካርታው መሠረት ሊተገበሩ የሚገባቸው የሽግግር ፍትሕ የተቋማት ቅንጅታዊ አመራር መድረክ ማቋቋም ፣የትግበራ ቅደም-ተከተል ጥቅል ዕቅድ ማውጣት፣የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን፣የሕዝብን እንዲሁም የባለድርሻ አካላትን ድጋፍና የባለቤትነት ስሜት የሚያጠናክሩ ሥራዎችን የማከናወን ተግባሩ በታቀደለት ጊዜ አለመፈጸሙ አሳሳቢ ነው ብሏል ኮሚሽኑ፡፡
የተዘጋጁት ረቂቅ ሕጎችና ሰነዶችም ለሕዝብ ውይይት እስከ አሁን አለመቅረባቸው የሚሳስብ ጉዳይ እንደሆነ አስረድቷል፡፡
ያሬድ እንዳሻው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i




Comments