ጥቅምት 7 2018 - ኢትዮጵያ በተለያዩ ተቋማት ለሚዘረጉ መሠረተ ልማቶች እስከ አሁን ማስተር ፕላን እንደሌላት ተነግሯል
- sheger1021fm
- Oct 17
- 1 min read
አሁን ማስተር ፕላኑን የማዘጋጀቱ ስራ እንደተጀመረም ሠምተናል።
ከመሰረተ ልማት ዘርጋታ ጋር በተገናኘ እያጋጣሙ ያሉ ችግሮች አንዱ መነሻ ዘርፉን የተመለከተ ማስተር ፕላን አለመኖር እንደሆነ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ተናግሯል።
የትኛው መሰረተ ልማት በየት በኩል ይለፍ፣ የትኛውስ ምን ቦታ አገልግሎት ይስጥ? የሚለው በዚህ ፕላን የተደገፈ አይደለም ሲሉ፤ የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ ኢትዮጵያ በዴቻ ተናግረዋል።
አሁን ይህን ማስተር ፕላን ለማዘጋጀት ስራዎች ተጀምረዋል ያሉን አቶ ኢትዮጵያ መሰረተ ልማቶቹን የሚዘረጉ ተቋማት በስራው መሳተፋቸውንም ነግረውናል።
ተቋማቱ ማስተር ፕላኑን በማዘጋጀቱ ሂደት ከመሳተፍ ባሻገር ሃብት እና ባለሞያ ማዋጣታቸውንም ጠቅሰዋል።
በስራው እየተሳተፉ ያሉ ሞያተኞች ማስተር ፕላኑን የማዘጋጀቱን ተግባር ከግማሽ በላይ ከውነዋል ያሉን ስራ አስፈጻሚው ፣ ቢበዛ እስከ ሁለት ዓመት ባለ ጊዜ ይጠናቀቃል ሲሉ አክለዋል።
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ተቋማት መሰረተ ልማት ሲዘረጉ የተናበበ አካሄድ እንዲከተሉ የማስተባበሩን ስራ እንደሚሰራም ነግሮናል።
ንጋቱ ረጋሣ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments