top of page

ጥቅምት 22፣2017 - በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ በተለምዶ ማሪያም ማዞሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የእሳት አደጋ በቤቶች ላይ ጉዳት አደረሰ

  • sheger1021fm
  • Nov 1, 2024
  • 1 min read

በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 በተለምዶ ማሪያም ማዞሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ፤ ዛሬ ከ6፡38 ገደማ ያጋጠመ የእሳት አደጋ በመኖሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት አደረሰ፡፡


በአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሞያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልተለየ ተጠጋግተው የተሰሩ የቆርቆሮ ቤቶች ተቃጥለዋል ብለዋል፡፡


አደጋውን ለመከላከል ከ70 በላይ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች፣ 12 የአደጋ መቆጣጠር መኪኖችን 2 ቦቴ መኪኖችን ተጠቅመዋል ተብሏል፡፡


የተያዘው ጥቅምት ወር ደረቅና ነፋሻማ በመሆኑ የእሳት አደጋን ያባብሳል ጥንቃቄ ሊደረግም ይገባል ሲሉ አቶ ንጋቱ ማሞ አሳስበዋል፡፡


ወንድሙ ሀይሉ

Recent Posts

See All
ታህሳስ 3/2018 የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ካለፈው ሃምሌ ወር ወዲህ እያደገ መጥቷል ተባለ።

ኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮች ከምታመርተው የኤሌክትሪክ ሃይል 90 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል እንደሆነ ተጠቅሷል። በዘንድሮው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት ኢትዮጵያ ከውሃ እና ከነፋስ ከ15,300 ጊጋዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨቷ ተነግሯል። በየወሩ በአማካይ 3,800 ጊጋዋት ሰአት የኤ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page