top of page

ጥቅምት 21፣2017 - የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ "ስማርት" ሲል የጠራቸውን ቅርንጫፎችን መከፈቱን ተናገረ

  • Oct 31, 2024
  • 1 min read

Updated: Nov 2, 2024

የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከ200 በላይ "ስማርት" ሲል የጠራቸውን ቅርንጫፎችን በተለያዩ አካባቢዎች መከፈቱን ተናገረ።


ይህም የባንኩ ደንበኞች ከወረቀት ንከኪ ነፃ በሆነ መንገድ ለዚህ አገልግሎት የተዘጋጁ ታብሌቶችን በመጠቀም ብቻ የባንክ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችል ነው ተብሎለታል።


በዚህም እንደ ገንዘብ ማስገባት፣ ማውጣትና ማስተላለፍ ያሉ አገልግሎቶችን ደንበኞች ዲጂታል በሆነ መንገድ ማግኘት የሚችሉበትን አሠራር ተዘርግቷል ተብሏል።


ባንኩ "ስማርት" ሲል በጠራቸው የባንክ ቅርንጫፎቹ ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣት፣ የሥራ ብቃትን መጨመር ብቻ ሳይሆን ባንኩ የደንበኞቹን ፍላጎት በቀላሉ ለማሟላት የሚያስችል፣ ባንኩን ምቹና ተመራጭ የሚየደርግ ነው ብሏል።


#የኦሮሚያ_ሕብረት_ሥራ_ባንክ ከ200 በላይ "ስማር" ሲል የጠራቸውን ቅርንጫፎችን መከፈቱን ባበሰረበት ሥነ - ሥርዓት ላይ የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደርቤ አስፋው እንዲሁም የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።


ከ13 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች አሉኝ ያለው የኦሮሚያ ሕብረት ስራ ባንክ የዲጂታል አገልግሎቱን ለማሳደግና በዲጂታል ፈጠራ ልቆ ለመገኘት በርካታ በፈጠራ የታገዙ አገልግሎቶችን ለደንበኞቹ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ተናግሯል።


ንጋቱ ሙሉ

Recent Posts

See All
ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡

ሐምሌ 21 2018 ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡ የዓሣ ምርቱ ወደ መሃል ሃገር እየተጫነ ለአዲስ አበባ ገበያ እየቀረበ ነውም ተብሏል፡፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ መገንባቱን ተከትሎ በተፈጠረው ንጋት ሰው ሰራሽ ሃይቅ በኢትዮጵያ ትልቁና ከ70 በላይ ደሴቶች ያሉት የውሃ አካል ነው፡፡ ከቅርብ

 
 
 
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 30.65 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ የኃይል ማስፋፊያ ዕቅድ ይፋ አደረገ።

ሐምሌ 20 2018 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 30.65 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ የኃይል ማስፋፊያ ዕቅድ ይፋ አደረገ። እቅዱ የኔትወርክ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ፣ የሰብስቴሽን እና ተያያዥ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች፣ ስማርት ግሪድ እና ቆጣሪ ማስፋፋትን እንደሚያካትት አገልግሎቱ ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page