top of page

ጥቅምት 20 2018የኮተቤ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ ፍሳሽ በመልቀቅ አካባቢን በክለዋል የተባሉ በገንዘብ ተቀጡ።

  • sheger1021fm
  • 3 hours ago
  • 1 min read
ree

የአዲስ አበባ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ወንዞችና የወንዞችን ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን 1.6 ሚሊዮን ብር መቅጣቱን ተናግሯል።


በየካ ክፍለ ከተማ፣ 3 ተቋማት የከብት እርባታ ፍሳሽን ቀጥታ ወደ ወንዝ በመልቀቅ፣ 3ቱም ማህበራት እያንዳንዳቸው 300,000 ብር በድምሩ 900,000 ብር መቀጣታቸው ተነግሯል።


የኮተቤ ዩኒቨርሲቲም ከፍተኛ ብክለት በመፈፀሙ 400,000 ብር እንዲቀጣ መደረጉንም ተቋሙ ተናግሯል።


በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ኢትዮ ቤስት ሪል ስቴት የተባለው ተቋምም ፈሳሽ ቆሻሻን ከወንዝ ጋር በማገናኘት ወንዞችንና ወንዝ ዳርቻዎችን መበከሉ ስተረጋገጠ 300,000 ብር ተቀጥቷል ተብሏል።


ወንዞችና የወንዞችን ዳርቻ ለታለመላቸው ልማት እዲውሉ የማድረግ ሀላፊነት አለብኝ ያለው ተቋሙ ህብረተሰቡ የደንብ መተላለፍ ሲያይ በነፃ ስልክ 9995 መረጃና ጥቆማ ይስጠኝ ብሏል።


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


 
 
 

Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡ ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበል

 
 
 
ጥቅምት 20 2018በፋብሪካ የተቀነባበሩ እንዲሁም ጤናማ ባልሆኑ ምግቦች ምክንያት የሚደርሱ የጤና ጉዳቶች ኢትዮጵያን ብዙ ወጪ እያስወጣት ነው ተባለ።

ሀገሪቱ በዚህ በየዓመቱ ከ31 ቢሊየን ብር በላይ ታወጣለች ተብሏል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተለወጠ የመጣው የአመጋገብ ሥርዓት ተላላፊ ያልሆኑ ህመሞች ጫና ከ52 በመቶ በላይ እንዲሆን ማድረጉ ተነግሯል። ይህንን ያስቀራል በሚል በዝግጅት ላይ ያለውን ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች የሚያጋልጡ ምግቦችን የሚቆጣጠር ረቂቅ አዋጅ

 
 
 
ጥቅምት 20 2018"ሰላም በሌለበት ኢንስትመንትም ሆነ የስራ እድል መፍጠር አይቻልም" ሲሉ የአዲስ አበባ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ዘሃራ ሞሃመድ ተናገሩ።

ፕሬዝዳንቷ ይህ የተናገሩት ዛሬ ጥቅምት 20 ቀን 2018 ዓ.ም "የንግድ ሚና ለሰላም ግንባታ'' በሚል ሃሳብ አዲስ አበባ የንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ባሰናዳው የፓናል ወይይት ላይ ነው። ለንግድ፣ ለኢንቨስትመንት ሆነ ለሌላ ስራ ሰላም መሰረት መሆኑን ያስረዱት ወ/ሮ ዘሃራ ሞሃመድ ያለ ሰላም ንግድን ማሰብ

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page