top of page

ጥቅምት 20 2018 - በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚበሩ መንገደኞች፤ የቲኬት ክፍያቸውን በቻፓ መፈፀም ይችላሉ ተባለ።

  • sheger1021fm
  • 5 hours ago
  • 1 min read

ይህንን ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት በኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በቻፓ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂስ መካከል በዛሬው ዕለት ተፈርሟል።


በስምምነቱ መሰረት በየትኛውም የአለም ክፍል የሚገኙ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኞች የበረራ ቲኬታቸውን በቻፓ የዲጂታል የክፍያ አቀላጣፊ መላ ተጠቅመው መፈፀም ይችላሉ ተብሏል።

ree

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ቻፓ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂስ አዠ ባደረጉት ስምምነት የማንኛውንም ባንክ ኤቲ ኤም (ATM) ካርድ በበይነ መረብ ላይ በመጠቀም የበረራ ትኬትን መግዛት ያስችላል ተብሏል፡፡


በአየር መንገዱ በይነ መረብ እና የስልክ መተግበሪያ (mobile app) አማካኝነት የማንኛውንም ባንክ ኤቲ ኤም (ATM) ካርድ መለያ ቁጥርን በመጠቀም የበረራ ትኬትን መግዛት የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋታቸዉን ተጠቅሷል፡፡


ስምምነቱ የበረራ ክፍያዎችን ለመፈጸም ቀላል፣ አስተማማኝ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ነው ተብሎለታል።


"የአየር በረራን በፊንቴክ - Flight Meets Fintech" የሚል መሪ ቃልም ተሰጥቶታል፡፡


ስምምነቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆሊዴይ እና ዲጂታል ሽያጭ ምክትል ፕሬዘዳንት  አቶ ሀይለመለኮት ማሞ እና የቻፓ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ናኤል ኃይለማርያም ፈርመውታል።


የኢትዮጵያ የአር መንገድ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ከሌሎች የዲጂታል የክፍያ አቀላጣፊዎች ጋር አብሮ ለመስራት መስማማቱ ይታወሳል።


ከግዙፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በክፍያ አቀላጣፊነት አብሮ ለመስራት የተፈራረመው ቻፓ እስካሁን ድረስ ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ክፍያዎችን ማስተላለፋ ተጠቅሷል።

Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - በሥራቅ አርሲ ዞን ባለንበት በጥቅምት ወር ብቻ 25 ሰዎች መገደላቸውን፣ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ተናገረ።

በኦሮሚያ ክልል በሥራቅ አርሲ ዞን ባለንበት በጥቅምት ወር ብቻ 25 ሰዎች መገደላቸውን፣ ይህንንም የተመለከተው በከባድና ጥልቅ የኃዘን ስሜት መሆኑን ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ተናገረ። ቋሚ ሲኖዶስ በኦሮሚያ  ክልል በምሥራቅ አርሲ ዞን አስተዳደር በጉና፣ በመርቲ፤ በሸርካ እና በሆሎንቆ ዋ

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page