ጥቅምት 18 2018 - በቢሾፍቱ የሚገነባው አዲሱ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት፤ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ከፍታ ምክንያት የነበሩ ችግሮችን የሚፈታ ነው ተባለ።
- sheger1021fm
- Oct 28
- 1 min read
የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በከፍታ ቦታ ላይ በመገኘቱ አውሮፕላኖች ብዙ ነዳጅ ጭነው ለመነሳት ይቸገሩ ነበር ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ።
ይህም ለምሳሌ ወደ ዋሺንግተን ዲሲ በሚደረግ በረራ በቂ ነዳጅ ይዞ መነሳት ስለማይችል ከቦሌ የሚነሳ አውሮፕላን ደብሊን ላይ አርፎና ነዳጅ ሞልቶ ለመነሳት ይገደዳል ብለዋል።

በቢሾፍቱ የሚገነባው አዲሱ ኤርፖርት ግን ከቦሌ ዝቅ ባለ ከፍታ ላይ የሚገኝ ስለሆነ ይህንን ችግር ይፈታል ብለዋል።
ግንባታው ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ ከ100 ሚሊየን በላይ መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል የተባለው አዲሱ ኤርፖርት ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ቀዳሚ አየር መንገድ ብቻ ሳይሆን ቀዳሚ ኤርፖርት ባለቤትም ያደርጋታል ብለዋል።
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments