top of page

ጥቅምት 17 2018 - በዩኔስኮ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የጽሑፍ ቅርሶች አስመዝጋቢ ኮሚቴ ሥራ ጀምሯል።

  • sheger1021fm
  • 1 hour ago
  • 1 min read

ኮሚቴው የኢትዮጵያን አብያተ መዛግብት እና ታሪካዊ መጻሕፍትን በዩኔስኮ የዓለም የትውስታ ማህደር (Memory of the World) ላይ ያስመዘግባል ተብሏል።


ኢትዮጵያ ከ20 ዓመታት በፊት 12 የሚደርሱ ጥንታዊ ፅሑፍና መዛግብቶቿን የዓለም የትውስታ ማህደር ላይ አስመዝግባለች።


ይሁን እንጂ ሀገሪቷ ካላት ሰፊና  የረጅም ዘመናት የሥነ ፅሑፍ ታሪክ አንፃር የተመዘገቡት  ከቁጥር የሚገቡ አይደሉም ተብሏል።


ለዚህም ሲባል ኮሚቴ አቋቁሞ መስራት አስፈላጊ መሆኑ ተነግሯል።

ree

ከአንድ ዓመት በፊት ተቋቁሞ  የተባበሩት መንግስታት የሳይንስ ትምህርትና የባህል ማዕከል(UNSCO) ተወካይእና የቱሪዝም ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ሥራ የጀመረው ኮሚቴው ሁለት ተጨማሪ መዛግብቶችን ለማስመዝገብ ተቃርቤያለሁ ብሏል።


ንጋት መኮንን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page