top of page

ጥቅምት 17 2018 - በአዋሽ ፈንታሌ የመሬት መንቀጥቀጥ አጋጠመ።

  • sheger1021fm
  • 4 hours ago
  • 1 min read

የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.8 ሆኖ የተመዘገበ ነበርም ተብሏል።


የመሬት መንቀጥቀጡ የተሰማው ትናንት ጠዋት 2 ሰዓት ከ24 ደቂቃ(2:24)ላይ እንደነበረም ተነግሯል።


ይህንን የነገሩን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊቪክስ፣ ስፔስ ሳይንስ እና የአስትሮኖሚ ተቋም ተመራማሪ አታላይ አየለ(ፕ/ር) ናቸው።

በፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱም በአዲስ አበባ፣ አዳማ ደብረሲና እና የአዋሽ ከተሞች የደረሰ ነበርም ብለውናል።


በአዋሽ ፈንታሌ ባሳለፍነው አርብም የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበረም ነግረውናል።


መሬት በማያቋርጥ እንቅስቃሴ ውስጥ ስላለች የመሬት መንቀጥቀጥ የሚከሰትበቀት ጊዜ በርግጠኝነት መናገር እንደሚቸግርም አስረድተዋል።


በተለይም የመሬት መንቀጥቀጥ በሚደጋገምባቸው አካባቢዎች ህንፃዎች ሲሰሩ መሰረታቸው እንዲጠናከሩም መክረዋል።


ወንድሙ ሀይሉ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page