top of page

ጥቅምት 17 2018 - በአዋሽ ፈንታሌ የመሬት መንቀጥቀጥ አጋጠመ።

  • Oct 27, 2025
  • 1 min read

የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.8 ሆኖ የተመዘገበ ነበርም ተብሏል።


የመሬት መንቀጥቀጡ የተሰማው ትናንት ጠዋት 2 ሰዓት ከ24 ደቂቃ(2:24)ላይ እንደነበረም ተነግሯል።


ይህንን የነገሩን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊቪክስ፣ ስፔስ ሳይንስ እና የአስትሮኖሚ ተቋም ተመራማሪ አታላይ አየለ(ፕ/ር) ናቸው።

በፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱም በአዲስ አበባ፣ አዳማ ደብረሲና እና የአዋሽ ከተሞች የደረሰ ነበርም ብለውናል።


በአዋሽ ፈንታሌ ባሳለፍነው አርብም የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበረም ነግረውናል።


መሬት በማያቋርጥ እንቅስቃሴ ውስጥ ስላለች የመሬት መንቀጥቀጥ የሚከሰትበቀት ጊዜ በርግጠኝነት መናገር እንደሚቸግርም አስረድተዋል።


በተለይም የመሬት መንቀጥቀጥ በሚደጋገምባቸው አካባቢዎች ህንፃዎች ሲሰሩ መሰረታቸው እንዲጠናከሩም መክረዋል።


ወንድሙ ሀይሉ

Recent Posts

See All
የመንግስት ግዥ አገልግሎት በዘንድሮው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች ንብረቶች የተገኘ ወደ 323 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመንግስት ገቢ አድርጌያለሁ አለ፡፡

ግንቦት 17/2018 የመንግስት ግዥ አገልግሎት በዘንድሮው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች ንብረቶች የተገኘ ወደ 323 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመንግስት ገቢ አድርጌያለሁ አለ፡፡ አገልግሎቱ ይህን ያህል ገንዘብ ዘጠኝ ወራት ውስጥ ለመንግስት ገቢ ሲያደርግ በታሪኩ የአሁኑ የጀመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page