top of page

ጥቅምት 11 2018 - በዓለም ዙሪያ በየቀኑ ከ100,000 በላይ የአየር በረራ እንደሚደረግ ይነገራል።

  • Oct 21, 2025
  • 1 min read

በኢትዮጵያም በቀን የሚነሳና የሚያርፈው እንዲሁም በኢትዮጵያ የአየር ክልል የሚተላለፈው በረራ ከ600 በላይ ደርሷል።


ከዚህ ሁሉ የአየር በረራ ጀርባ ሆነው፣ የበረራውን ደህንነት፣ አዋጭነትና ቅልጥፍና የሚቆጣጠሩት #የአየር_ትራፊክ_ተቆጣጣሪዎች ናቸው።


ያለነሱ ከአደጋ ነፃ የሆነ እና የሰመረ የአየር በረራን ማሰብ ከባድ እንደሚሆን ይነገራል።


በዚህም ምክንያት የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ሚናን፣የአቪኤሽን ዘርፍ የልብ ምት ነው እንዲባል ያደርገዋል።

በሌላ በኩል ስራው ባለው ውጥረትና ጭንቀት ምክንያት በዓለም ዙሪያ ከባድ ከሆኑ የሙያ አይነቶች አንዱ ያደርገዋል።


ጥቅምት 10 በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ስራ የሚታሰብበት፣ተገቢው ክብር የሚሰጥበት ዕለት ነው።


የኢትዮጵያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ማህበርም ቀኑን አስቦት ውሏል።


በዓለም ዙሪያ በዚህ ሙያ ለተሰማሩት ባለሙያዎች የሚሰጠው ክብርና የሚያገኙት ክፍያ ከፍተኛ መሆኑ የተነሳ ሲሆን በኢትዮጵያ ግን ባለሙያዎቹ ለስራቸው የማይመጥን በጣም ዝቅተኛ ደምወዝ ተከፋይ መሆናቸው ተነግሯል።


ለዚህ ሙያ ከአፍሪካም ዝቅተኛውን ክፍያ የምትከፍለው ሀገር ኢትዮጵያ መሆኗም ሲነገር ሰምተናል።


በዚህም ምክንያት ሰራተኛው በየጊዜው ከተቋሙ ስለሚለቅ ብዙ ልምድ የሚጠይቀው የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪነት ሙያ ልምድ ያለውና ለረጅም ጊዜ የሚያገለግል ባለሙያ እንዲያጣ ሆኗል ተብሏል።


እለቱን ምክንያት በማድረግም ከዚህ ጋር የተገናኙ ለዓመታት የሚነሱ ጥያቄዎች መልስ እንዲያገኙ ተጠይቋል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..


ቴዎድሮስ ወርቁ

Recent Posts

See All
በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ።

ነሐሴ 7 2018 በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ። ከአስር ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የታየው የኤልኒኖ ተፅዕኖ የእህል ምርት ውጤትን ከ15 እስከ 20 በመቶ እንዲቀንስ አድርጎ እንደነበር አንድ የዘርፉ ተመራማሪ ነ

 
 
 
የኤሌክትሪክ ታሪፍ በየጊዜው ሲጨምር ይታያል፡፡

ነሐሴ 7 2018 የኤሌክትሪክ ታሪፍ በየጊዜው ሲጨምር ይታያል፡፡ በዚህም ደንበኞች ቅሬታ ያቀርባሉ ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በበኩሉ አዲስ የታሪፍ ጭማሪ አለማድረጉን፤ የአሁኑ የዋጋ ለውጥ ከ2017 ጀምሮ በ16 ዙር ለማስፈጸም የታቀደው አሰራር አካል ነው ብሏል፡፡ እንደውም ከሁለት አመት በፊት ተግባራዊ ያ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page