top of page

ጥር 9፣ 2015- የጀርመኗ የመከላከያ ሚኒስትር ክርስቲን ላምበሬችት በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣናቸውን መልቀቃቸው ተሰማ

  • Jan 17, 2023
  • 1 min read

የጀርመኗ የመከላከያ ሚኒስትር ክርስቲን ላምበሬችት በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣናቸውን መልቀቃቸው ተሰማ፡፡


የመከላከያ ሚኒስትሯ ከ2 ሳምታት በፊት በዘመን መለወጫው ባስተላለፉት መልዕክት ለዩክሬይን በጦር እርዳታነት 5000 የወታደር ቆቦችን እንልካለን ማለታቸው ለትችት ዳርጓቸው መቆየቱን ዘጋርዲያን ፅፏል፡፡


ከዚህም በተጨማሪ የጀርመንን ጦር በማዘመኑ ረገድ ዳተኛ ሆነዋል በሚል እየተነቀፉ እንደሆነ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


ከነዚህ ትችቶች በተጨማሪ በጦር ሄሊኮፕተር ልጃቸውን አንሸርሽረዋል መባላቸውም እያስወረፋቸው ነው፡፡


ጀርመን ለዩክሬይን ዘመን አፈራሽ ታንኮችን እንድትሰጥ ጉትጎታ እንደበዛባት ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
የሐምሌ 20 የውጭ ሀገር ወሬዎች

#ቀይ_ባህር በቀይ ባህር የባብኤል መንደብ ወሽመጥ የሚተላለፉ መርከቦች ብዛት በእጅጉ እየቀነሰ ነው ተባለ፡፡ በወሽመጡ የሚተላለፉ መርከቦች ብዛት የቀነሰው የየመን ሁቲዎች ባለፈው ሳምንት የሳውዲ አረቢያን ወደቦች እንከቻችምባታለን ብለው ከዛቱ በኋላ እንደሆነ ሬውተርስ ፅፏል፡፡ ለምሳሌም ትናንት በባብኤል መንደብ የባህ

 
 
 
የሐምሌ 17 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ብሪታንያ የብሪታንያ መንግስት በኬንያ ላካሂድ የነበረውን አመታዊ የጦር ልምምድን ትቼዋለሁ አለ፡፡ የብሪታንያ ሰራዊት አመታዊ የኬንያ የጦር ልምምዱን የተወው ከምስራቅ አፍሪካዊቱ አገር መንግስት ፈቃድ ባለማግኘቱ ነው መባሉን አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ የብሪታንያ ጦር ከዚህ ቀደም በኬንያ በየአመቱ በመደበኛነት የጦር ልም

 
 
 
የሐምሌ 16 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሊቢያ በሊቢያ የተለያዩ የፖለቲካ ማህበራት አገሪቱ ወደ አንድነቷ እንድትመለስ ጥሪ አቀረቡ፡፡ የፖለቲካ ማህበራቱ በጋራ የህውደት ጥሪውን ያቀረቡት የሊቢያን የወደፊት እጣ ፈንታ በተመለከተ ምክክር ባደረጉበት ወቅት እንደሆነ TRT አፍሪካ ፅፏል፡፡ በሊቢያ የቀድሞው መሪ የኮሎኔል ሙአመር ጋዳፊ አስተዳደር ከ15 አመታት

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page