top of page

ጥር 6፣ 2015የብራዚሉ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጂየር ቦልሶናሮ አመፅ በማነሳሳት ምርመራ ሊካሄድባቸው ነው

  • Jan 14, 2023
  • 1 min read

የብራዚሉ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጂየር ቦልሶናሮ አመፅ በማነሳሳት ምርመራ ሊካሄድባቸው ነው፡፡


ቦልሶናሮ ምርመራ የሚካሄድባቸው ባለፈው ሳምንት እሁድ በሺህዎች የሚቆጠሩ ነውጠኛ ደጋፊዎቻቸው በርዕሰ ከተማዋ ብራዚሊያ ፓርላማው ፣ ቤተ መንግስቱን እና የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሕንፃዎች በወረሩበት ድርጊት እንደሆነ SBS ፅፏል፡፡


የቀድሞው ፕሬዝዳንት በጥቅምት ወር በተካሄደው ዳግም ምርጫ በግራ ክንፈኛው ሉላ ኢናሲዮ ዴ ሲልቫ በጠባብ ልዩነት መሸነፋቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡


ቦልሶናሮ ግን ሉላ አልተመረጠም የሚል የቪዲዮ ምስል አሰናድተው እዩልኝ ብለው ነበር፡፡


ይህም ህጋዊውን ምርጫ ዋጋ ለማሳጣት የተደረገ የአመፅ ማነሳሻ ተደርጎ መቆጠሩ ተሰምቷል፡፡


ጂየር ቦልሶናሮ በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ ይገኛሉ፡፡


ምርመራው ሌሎችንም የቀድሞ ባለስልጣናት ጭምር ይመለከታል ተብሏል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
የሐምሌ 20 የውጭ ሀገር ወሬዎች

#ቀይ_ባህር በቀይ ባህር የባብኤል መንደብ ወሽመጥ የሚተላለፉ መርከቦች ብዛት በእጅጉ እየቀነሰ ነው ተባለ፡፡ በወሽመጡ የሚተላለፉ መርከቦች ብዛት የቀነሰው የየመን ሁቲዎች ባለፈው ሳምንት የሳውዲ አረቢያን ወደቦች እንከቻችምባታለን ብለው ከዛቱ በኋላ እንደሆነ ሬውተርስ ፅፏል፡፡ ለምሳሌም ትናንት በባብኤል መንደብ የባህ

 
 
 
የሐምሌ 17 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ብሪታንያ የብሪታንያ መንግስት በኬንያ ላካሂድ የነበረውን አመታዊ የጦር ልምምድን ትቼዋለሁ አለ፡፡ የብሪታንያ ሰራዊት አመታዊ የኬንያ የጦር ልምምዱን የተወው ከምስራቅ አፍሪካዊቱ አገር መንግስት ፈቃድ ባለማግኘቱ ነው መባሉን አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ የብሪታንያ ጦር ከዚህ ቀደም በኬንያ በየአመቱ በመደበኛነት የጦር ልም

 
 
 
የሐምሌ 16 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሊቢያ በሊቢያ የተለያዩ የፖለቲካ ማህበራት አገሪቱ ወደ አንድነቷ እንድትመለስ ጥሪ አቀረቡ፡፡ የፖለቲካ ማህበራቱ በጋራ የህውደት ጥሪውን ያቀረቡት የሊቢያን የወደፊት እጣ ፈንታ በተመለከተ ምክክር ባደረጉበት ወቅት እንደሆነ TRT አፍሪካ ፅፏል፡፡ በሊቢያ የቀድሞው መሪ የኮሎኔል ሙአመር ጋዳፊ አስተዳደር ከ15 አመታት

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page