top of page

ጥር  29፣2016 - የአፍሪካ ቡና ሳምንት አውደ ርዕይ በሚሊኒየም አዳራሽ ተከፈተ

  • Feb 7, 2024
  • 1 min read

የኢትዮጵያን ቡና በአለም አቀፍ ደረጃ ለማስታወዋወቅና የገበያ እድል ለመፍጠር ይረዳል የተባለ ለ4 ቀን የሚቆይ የአፍሪካ ቡና ሳምንት አውደ ርዕይ በሚሊኒየም አዳራሽ ተከፈተ፡፡

 

በአውደ ርዕይው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አዱኛ ደበላ በኢትዮጵያ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከ20 ሚሊየን በላይ ሰዎች በቡና ላይ ሕይወታቸውን መስርተዋል ብለዋል፡፡

 

በአለም አቀፍ ደረጃ የቡና ዋጋ እየቀነሰ ቢመጣም ኢትዮጵያ ግን በ2016 1.4 ቢሊየን ዶላር በ2015 ደግሞ 1.3 ቢሊየን ዶላር አግኝታለች ሲሉ አስረድተዋል፡፡

 

ለዚህም ምክንያት በቀደመዉ አሰራር ላይ ማሻሻያ መደረጉ፣ የቁጥጥር ስራው የበረታ መሆኑ እንዲሁም  ባለስልጣኑ ከፍተኛ ትኩረት ለቡና ጥራት መስጠቱ  ከሚበዙት ጥቂቶቹ ናቸዉ ተብሏል፡፡

 

መድረኩ የቡና ልማት ላይ ያሉ ተዋንያኖች ገፅ ለገፅ የሚመክሩበትና የሚወያዩበት እንደሚሆን ተሰምቷል፡፡

 

በአውደ ርዕዩ ላይ የተለያዩ አለም አገራት ቡና ላኪዎች ተቀባዮች እና አርሶ አደሮች ተገኝተዋል፡፡

 

ይህም ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ቡና እንድታስተዋውቅ እድል ይሰጣል ተብሏል፡፡

 

በ4 ቀን በሚቆየው አውደ ርዕይ ቡና ላይ ያሉ ችግሮች ምንድናቸው እና እንዴት ይፈታሉ የሚሉ ፁሁፎች ይቀርባሉ ተብሏል፡፡

 


ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አገራት ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ቡና ጠጪ ያለባት አገር ነች ተብሏል፡፡

 

በዚህም በአፍሪካ አህጉር ከሚጠጣው ቡና 50 በመቶ የሚሆነው በኢትዮጵያዊያን እንደሆነ ተነግሯል፡፡

 

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን በተያዘው በጀት ዓመት 1.75 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት አስታውሷል፡፡

 

 

ያሬድ እንዳሻው

 

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 




Recent Posts

See All
የሐምሌ 23 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ግብፅ በግብፅ የሜዴትራኒያን የባህር ዳርቻ የነበረ የአሜሪካ የጋዝ ማጠራቀሚያ መርከብ በድሮን ተመታ ተባለ፡፡ ሁለት የደህንነት ምንጮች መርከቡ በድሮን እንደተመታ አረጋግጠውልኛል ሲል ሬውተርስ ፅፏል፡፡ መርከቡ በድሮን እንደተመታ በእሳት መያያዙ ታውቋል፡፡ ቃጠሎው ወደ ሌላ መርከብም ተጋብቶ ነበር ተብሏል፡፡ ኋላ ግን

 
 
 
የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ማሳደግ፣አፍሪካዊያን የጋራ መጪ እድላቸውን እንዲቀርፁ ማገዝ ያስፈልጋል ተባለ።

ሐምሌ 23 2018 የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ማሳደግ፣አፍሪካዊያን የጋራ መጪ እድላቸውን እንዲቀርፁ ማገዝ ያስፈልጋል ተባለ። የአፍሪካ ሀገሮች እርስ በእርስ፣በአፍሪካና በሩሲያ እንዲሁም አፍሪካ ከተቀረው ዓለም ጋር ያላትን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ማሳደግን ዓለማው ያደረገ ዓለም አቀፍ ጉባኤ በተባበሩት መንግስታት የአ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page