top of page

ጥር 24፣2016 - በአማራ ክልል የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአራት ወራት መራዘሙ ተነገረ

  • sheger1021fm
  • Feb 2, 2024
  • 1 min read

በአማራ ክልል የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአራት ወራት መራዘሙ ተነገረ፡፡


በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ዛሬ ውይይት አድርገውበታል ተበሏል፡፡


በዚህም ተጨማሪ ስራዎች በመኖራቸው አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለተጨማሪ 4 ወራት ማራዘም ማስፈለጉ ተነግሯል፡፡


የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የጸደቀው በሁለት ተቃውሞ በሶሰት ድምፅ ተአቅቦና በአብላጫ ድምፅ እንደሆነ ኢቢሲ ዘግቧል፡፡


በአማራ ክልል ለ6 ወር ታውጆ የነበረውና በመተገበር ላይ ያለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመጪው ማክሰኞ 6 ወሩን ይደፍናል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page