የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ እስከ ስምንት ብር ጭማሪ ተደረገ፡፡
- sheger1021fm
- 8 minutes ago
- 1 min read
ታህሳስ 1 2018
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ እስከ 8 ብር ጭማሪ ተደረገ፡፡
ጭማሪው ከዛሬ 6:00 ጀምሮ ተግባረዊ የተደረገ መሆኑን የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስረድቷል፡፡
በጭማሪው መሰረት በቤንዚን ላይ የ7 ብር ገደማ ጭማሪ ሲደረግ በኬሮሲን ላይ ደግሞ የ8 ብር ገደማ ጭማሪ ተድርጓል፡፡

ቤንዚን፣ የኬሮሲን እና ነጭ ናፍጣ የሦስቱም የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በአዲሱ ጭማሪ መሰረት 129.12 ብር እንዲሆኑ ተድርጓል።
ከሰሞኑ በዲስ አበባ ሆነ በክልሎች የነዳጅ ማደያዎች ነዳጅ የለንም ብለው ረጃጅም የተሽከርካሪ ሰልፎች ታይተው ቆይተዋል፡፡
ለዚህም ከታሕሳስ ወር አንስቶ የቫት እና የኤክሳይስ ታክስ በአጠቃላይ የ30 በመቶ ግብር ይጣላል የሚል ምክንያት በብዙዎች ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዛሬ ለነዳጅ አስጪዎች በላከው የዋጋ ጭማሪ ደብዳቤ ላይ ግን የታክስ ጭማሪን በተመለከተ ያለው ነገር የለም።












Comments