top of page

ጥር 22፣ 2015- ስዊድን የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት /ኔቶ/ አባል የመሆን ጥረቷን ለጊዜው መግታቷን የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቶቢያስ

  • sheger1021fm
  • Jan 30, 2023
  • 1 min read

ስዊድን የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት /ኔቶ/ አባል የመሆን ጥረቷን ለጊዜው መግታቷን የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቶቢያስ ቢልስቶርም ተናገሩ፡፡


ስዊድን ነባር የኔቶ አባል ከሆነችው ቱርክ ጋር ቅራኔዋ እየተባባሰ መምጣቱ የቃል ኪዳን ድርጅቱ አባል የመሆን ጥረቷን ለጊዜው እንድትገታው ማስገደዱን ቢል ስቶርም ተናግረዋል፡፡


ስዊድን እና ፊንላንድ የኔቶ አባላት ለመሆን በጣምራ ማመልከቻ ያቀረቡት ባለፈው አመት ነው፡፡


ሁለቱ አገሮች የኔቶ አባላት ለመሆን በጦር ቃል ኪዳን ድርጅቱ 30ውም አባል አገሮች መደገፍ ይኖርባቸዋል፡፡


ባለፈው ሳምንት የቱርኩ ፕሬዘዳንት ሪቺፕ ታይፕ ኤርዶአን ስዊድን በጭራሽ ድጋፋችንን አትጠብቅ ማለታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡


የስዊድኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጉዳዩን ዳግም ለማንቀሳቀስ ትንሽ እንጠብቃለን ማለታቸውን CGTN ፅፏል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Recent Posts

See All
ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎች ምርቶች እና አገልግሎቶቻቸውን የሚጠቀሙ ሰዎች ጋር ለመድረስ እንደሚቸገሩ ይናገራሉ፡፡

ጥር 14/2018   ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎች ምርቶች እና አገልግሎቶቻቸውን የሚጠቀሙ ሰዎች ጋር ለመድረስ እንደሚቸገሩ ይናገራሉ፡፡   ለዚህም ተስማሚ የሽያጭ ቦታ በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት አለመቻል፣ የበጀት እጥረትን ጨምሮ ሌሎች ችግሮች እንደሚያጋጥሟቸው ይሰማል፡፡   ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች የሚገጥማቸውን ችግር ያቀላል፣ ም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page