top of page

ግንቦት 5፣2017 - የነዳጅ ክፍያን በዳሽን ባንክ የሞባይል መተግበሪያ ወይንም "ዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ "መክፈል ተጀመረ።

  • May 13, 2025
  • 1 min read


የዳሸን ባንክ ደንበኞቹ የነዳጅ ክፍያቸውን በቀላሉ የሚፈፅሙበትን ዲጂታል የክፍያ አማራጭ ማቅረቡን ባንኩ ተናግሯል።


ባንኩ ደንበኞቼ በተመረጡ የነዳጅ ማደያዎች ነዳጅ ሲቀዱ ክፍያቸውን በዳሸን ሱፐር አፕ በሶስት ክሊክ ብቻ መፈጸም ይችላሉ ብሏል።


በቅርቡም ዳሸን ባንክ ይህንን አገልግሎት በሁሉም ማደያዎች እጀምራለሁ ሲል አስረድቷል፡፡


የዳሸን ባንክ ደንበኞች የዳሸን ሱፐርአፕ መተግበሪያ ውስጥ በመግባት በሚኒ አፕ መተግበሪያ ውስጥ የሚገኘውን የነዳጅ ክፍያ (Fuel Payment) አማራጭ በመምረጥ የሚላክላቸውን የነዳጅ ክፍያ ኮድ በማስገባት ለገዙት ነዳጅ ከፍያቸውን መፈፀም ይችላሉ ተብሏል።


ወይንም ደግሞ በአማራጭነት የቀረበውን የኪው አር ኮድ ስካን በማድረግ በቀላሉ ክፍያቸውን ወዲያውኑ መፈፀም ይችላሉ ሲል ባንኩ አስረድቷል ፡፡


የነዳጅ ግብይቱን ለማዘመን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ያበለጸገዉን የነዳጅ ስርጭት መከታተያ መተግበሪያ ከዳሸን ሱፐር አፕ ጋር በማጣጣም የነዳጅ ክፍያ መፈፅም እንዲያስችል ተደርጎ ተዘጋጅቷል ተብሏል፡፡


ዳሸን ባንክ ከነዳጅ ማደያ ባለቤቶች ጋር በተለያዩ ዘርፎች በጋራ ለመስራት ዝግጅት እያደረገ እንደሆነም አስረድቷል፡፡


ዳሸን ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ የመጀመሪያ ነው ያለውን‘’ ሱፐር አፕ’’ ለአገልግሎት ወደ ስራ ማስገባቱን መናገሩ ይታወሳል።


የዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ የያዘ እና ዘመናዊ አገልግሎት ማቅረብ የሚያስችል መተግበሪያ መሆኑ ተጠቅሷል።


የነዳጅ ክፍያ አማራጩም በዚሁ መተግበሪያ ላይ መቅረቡ የተነገረ ሲሆን አጠቃቀሙም ቀላል ነው ተብሎለታል፡፡


ተህቦ ንጉሴ

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ በተጠናቀቀው በበጀት አመት 117 ሺህ ህፃናት ተወልደው የልደት ማረጋገጫ ሰጥቻቸዋለው ሲል የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ተናገረ፡፡

ሐምሌ 21 2018 በአዲስ አበባ በተጠናቀቀው በበጀት አመት 117 ሺህ ህፃናት ተወልደው የልደት ማረጋገጫ ሰጥቻቸዋለው ሲል የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ተናገረ፡፡ ይህም ህፃናቱ ተወልደው በ90 ቀናት ውስጥ የተመዘገቡ ናቸው ሲሉ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ዮሴፍ ንጉሴ አስረድተዋል፡፡ ዘግይተው

 
 
 
ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡

ሐምሌ 21 2018 ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡ የዓሣ ምርቱ ወደ መሃል ሃገር እየተጫነ ለአዲስ አበባ ገበያ እየቀረበ ነውም ተብሏል፡፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ መገንባቱን ተከትሎ በተፈጠረው ንጋት ሰው ሰራሽ ሃይቅ በኢትዮጵያ ትልቁና ከ70 በላይ ደሴቶች ያሉት የውሃ አካል ነው፡፡ ከቅርብ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page