top of page

ግንቦት  5፣2016 - ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፉ ሀብት ቢኖራትም አውጥታ መጠቀም አለመቻሏ ብዙ እያሳጣት ነው ተባለ

  • May 13, 2024
  • 1 min read

ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፉ ሀብት ቢኖራትም አውጥታ መጠቀም አለመቻሏ ብዙ እያሳጣት ነው ተባለ፡፡

 

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አዘጋጅቶ እያተደረገ ባለው ኢትዮጵያ ታምርት ኤግዚቢሽን ላይ ዘርፉን ለማሳደግ ምክክሮች ጎን ለጎን እየተደረገ ሲሆን በተለይም ከኃይል አቅርቦትና ተደራሽነት እንዲሁም ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፉ ያላት ሀብት አውጥቶ ለገብያ ከማቅረብ አኳያ ያለባት ክፍተት ተነስቷል፡፡

 

የማዕድን ሚኒስትር አቶ ሃብታሙ ተገኝ እንዳሉት ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፉ ሀብት ቢኖራትም አውጥታ ግን እየተጠቀመችበት አይደለም፡፡

 

እያወጣች የምትጠቀምባቸው ውስን የማዕድን ሀብቶችም ቢሆኑ እሴት እየጨመረች ከመላክ ይልቅ በጥሬ እቃ ነው የምትልከው ያሉት ሚንስትሩ ይህ ነገር ከፍተኛ ገቢ እያሳጣ ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትርክ ኃይል ስራ አስፈጻሚ  አሸብር ባልቻ(ኢ/ር) በበኩላቸው ሀገሪቱ አሁን ላይ በኃይል አቅርቦት ችግር እየገጠማት ባይሆንም ፍላጎቶች በየጊዜው በዚህ ልክ የሚጨምሩ ከሆነ የከፋ የኃይል እጥረት በቅርቡ ሊያጋጥማት ይችላል ይላሉ፡፡

 

ይህንን ችግር ለመቅረፍ ከወዲሁ የሀይል መስመሮችን ከማደስ ባለፈ በዘርፉ የግል ተቋማት እንዲገቡ ሊደረግ ይገባል ብለዋል፡፡

 

መንግስት ከውጪ የሚመጡ አልሚዎችን እርካሽ የኃይል አቅርቦት አለ እያለ ቢያመጣም መሰረተ ልማት ባለመሟላቱ ብዙ አልሚዎች ለኪሳራ እየተዳረጉ ነው ሲሉ ኢንጅነር አሸብር ተናግረዋል፡፡

 

ከዚህም ባለፈ ኢንዱስትሪ አካባቢ ያለው የኃይል ታሪፍ ዋጋ ዝቅተኛ ነው ይህንን ለማስተካከል እየሰሩ መሆኑን የተናገሩት ኢንጅነሩ የታሪፍ ማስተካከያው ተግባራዊ ለማድረግ ስራዎች አሁን እየጨረስን ነው ብለዋል፡፡

 

የማዕድን ሚኒስትሩ አቶ ሀብታሙ በበኩላቸው በማዕድን ዘርፍ እሴት ጨምሮ ወደ ውጪ መላኩ ብዙ ወጪ የሚጠይቅ ቢሆንም ቢያንስ በከፊል እሴት ጨምሮ ወደ ገበያ እንዲቀርቡ ለማድረግ የሚያስችል ስራዎች አሁን ላይ እየሰራንበት ነው ብለዋል፡፡

 

ኢትዮጵያ ታምርት በሚል ስያሜ እየተካሄደ ያለው የሀገር ውስጥ አምራቾች የሚሳተፉበት ኤግዚቢሽን ዛሬ የሚጠናቀቅ ሲሆን ጎን ለጎን አምራች ዘርፉን የተሻለ ስራ እንዲሰራ ለማስቻል የሚረዱ ውይይቶች እንደተካሄዱበት ሰምተናል፡፡

 

በረከት አካሉ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 

 

 

 

Recent Posts

See All
የነሐሴ 4 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሳውዲ_አረቢያ በሳውዲ አረቢያ ጂዛን በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ከባድ ቃጠሎ ተቅስቅሶ ነበር ተባለ፡፡ በጂዛኑ ማጣሪያ ላይ ቃጠሎ ተቅስቅሶ የነበረው ከባድ ፍንዳታ ከተሰማ በኋላ እንደሆነ አናዶሉ ፅፏል፡፡ በጁቢየል የተፈጥሮ ጋዝ ማሰናጃ ከተማም ቃጠሎ ተቀስቅሶ ነበር ተብሏል፡፡ የሳውዲ ምንጮች ቃጠሎዎቹ ተቀስቅሰው እ

 
 
 
በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡

ነሐሴ 4 2018 በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት በበኩሉ ሳያጠፋ የምንቀጣው አሽከርካሪ የለም እንዲያውም ሁሉንም ህጎች እናስከብር ብንል የማይቀጣ አሽከርካሪ አይኖርም ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.... ምህረት ስዩም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page