top of page

ግንቦት 30፣2016 - አጠቃላይ ባንኮች የሰጡት ብድር ከ2 ትሪሊዮን ብር በላይ ደርሷል

  • Jun 7, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ ያሉት ባንኮች ትርፋማነታቸው፣ ያላቸው ሀብት፣ ካፒታል፣ የቁጠባ መጠን እና በሌሎች አሃዛዊ መረጃዎች እየተጠቀሱላቸው በጥሩ ጎዳና ላይ መሆናቸው ሲነገር ይሰማል፡፡


ለአብነትም የባንኮች ተቀማጭ ከ 2.29 ትሪሊዮን ብር በላይ ደርሷል፡፡


በዚህ ዓመት ስድስት ወራት ብቻ ከ 124.2 ቢሊየን ብር በላይ አዲስ ተቀማጭ ገንዘብ ባንኮቹ ሰብስበዋል፡፡


አጠቃላይ ባንኮች የሰጡት ብድርም ከሁለት ትሪሊዮን ብር በላይ ደርሷል፡፡


ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ ባወጣው እና የባንኮችን ሁኔታ በሚያስረዳው ሪፖርቱ የሀገሪቱ ባንኮች ከሚሰጡት ብድር አብዛኛው የተከማቸው በጥቂት ተበዳሪዎች ነው ማለቱ ይታወሳል፡፡


ሆኖም ግን ባንኩ የሀገሪቱ ባንኮች በአብዛኛዎቹ መለኪያዎች ጤናማ ናቸው ይላል፡፡


ሸገር ያነጋገራቸው የምጣኔ ሀብት ባለሞያ የባንኮቹን ጤናማነት ከሚሰጡት አገልግሎትና ከደንበኞች እርካታ ጋር እያጣቀሱ የጤናማነታቸው እውነተኝነት ላይ ጥያቄ ያነሱበታል፡፡


ባለሞያው አቶ ያዕቆብ በቀለ የባንኮች የተቀማጭ መጨመር፤ ገንዘብ ከባንክ ውጪ እንደይሆን በመባሉ በግዴታም ጭምር ስለተደረገ መጨመሩን ተናግረዋል፡፡


‘’ብርን እንኳን በቀን ማውጣት የሚቻለው በገደብ ነው፣ ሰው ታሞ አንኳን 20 ሺህ ብር ስጡን ሲባሉ የማይሰጡ ብዙ ብንኮች አሉ’’ ሲሉ ይናገራሉ፡፡


ከኢትዮጵያ ሁሉም ባንኮች ብድር የወሰዱ ሰዎች ብዛት 350 ሺህ አካባቢ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡


ብሄራዊ ባንክ በቅርቡ ይፋ ባደረገው ሪፖርት ላይ እንደሰፈረውም የባንክ ብድሮች በጥቂት ተበዳሪዎች ጋር ተከማችቷል፡፡


ሪፖርቱ ላይ እንደተቀሰው ሁሉም ባንኮች እስከ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ድረስ ከሰጡት 1.9 ትሪሊዮን ብር ብድር ውስጥ 23.5 በመቶውን ያበደሩት ለአስር ተበዳሪዎ ብቻ ነው፡፡


ይህ እንዳለ ሆኖ አንዳንድ ባንኮች ደግሞ ለሀላፊዎቻቸው የሚሰጡትን ብድር ጤናማነት አቶ ያዕቆብ ይጠይቃሉ፡፡


ንጋቱ ሙሉ



Recent Posts

See All
ከአምስት አመት በኋላ በምግብ እጥረት ምክንያት የሚቀነጭሩ ህጻናት እንዳይኖሩ በሰቆጣ ቃል ኪዳን የገባችው ኢትዮጵያ እስካሁን በከወነችው ስራ ምን ውጤት አገኘች?

ሰኔ 15/2018 ከአምስት አመት በኋላ በምግብ እጥረት ምክንያት የሚቀነጭሩ ህጻናት እንዳይኖሩ በሰቆጣ ቃል ኪዳን የገባችው ኢትዮጵያ እስካሁን በከወነችው ስራ ምን ውጤት አገኘች? በ2025 ስራውን በ700 ወረዳዎች ላይ ተግባራዊ አደርጋለሁ ብትልም እዛ ማድረስ ግን አልቻለችም ታዲያ ከ አምስት አመት በኋላ እንደቃሏ

 
 
 
የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት (USAID)ን ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ስራቸውን ማቋረጣቸው እና እርዳታ መቀነሳቸው እያሳደረ ያለው ጫና ከፍ ያለ መሆኑ ይነገራል፡፡

ሰኔ 15/2018 የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት (USAID)ን ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ስራቸውን ማቋረጣቸው እና እርዳታ መቀነሳቸው እያሳደረ ያለው ጫና ከፍ ያለ መሆኑ ይነገራል፡፡ በእዚሁ ምክንያት የኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ግማሽ ያህል ሰራተኞቹን መቀነሱን እና የሰረዘው ፕሮጅክትም መኖሩን መናገ

 
 
 
በፀረ ተባይ ማምረቻና በሌሎችም ፋብሪካዎች መወገድ ሲኖርባቸው ከ2 እስከ 31 አመት ተከማችተው የሚገኙ አደገኛ ኬሚካሎች ክምችት መኖሩ ተነገረ ፡፡

ሰኔ 15/2018 በፀረ ተባይ ማምረቻና በሌሎችም ፋብሪካዎች መወገድ ሲኖርባቸው ከ2 እስከ 31 አመት ተከማችተው የሚገኙ አደገኛ ኬሚካሎች ክምችት መኖሩ ተነገረ ፡፡ የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ባካሄደው የክዋኔ ኦዲት በተለያዩ ሶስት ፋብሪካዎች ለአካባቢ ብክለት ምክንያት የሚሆኑ ከ69 ቶን በላይ የመጠቀሚያ ጊዜ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page