top of page

ግንቦት 30፣2016 - አጠቃላይ ባንኮች የሰጡት ብድር ከ2 ትሪሊዮን ብር በላይ ደርሷል

  • sheger1021fm
  • Jun 7, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ ያሉት ባንኮች ትርፋማነታቸው፣ ያላቸው ሀብት፣ ካፒታል፣ የቁጠባ መጠን እና በሌሎች አሃዛዊ መረጃዎች እየተጠቀሱላቸው በጥሩ ጎዳና ላይ መሆናቸው ሲነገር ይሰማል፡፡


ለአብነትም የባንኮች ተቀማጭ ከ 2.29 ትሪሊዮን ብር በላይ ደርሷል፡፡


በዚህ ዓመት ስድስት ወራት ብቻ ከ 124.2 ቢሊየን ብር በላይ አዲስ ተቀማጭ ገንዘብ ባንኮቹ ሰብስበዋል፡፡


አጠቃላይ ባንኮች የሰጡት ብድርም ከሁለት ትሪሊዮን ብር በላይ ደርሷል፡፡


ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ ባወጣው እና የባንኮችን ሁኔታ በሚያስረዳው ሪፖርቱ የሀገሪቱ ባንኮች ከሚሰጡት ብድር አብዛኛው የተከማቸው በጥቂት ተበዳሪዎች ነው ማለቱ ይታወሳል፡፡


ሆኖም ግን ባንኩ የሀገሪቱ ባንኮች በአብዛኛዎቹ መለኪያዎች ጤናማ ናቸው ይላል፡፡


ሸገር ያነጋገራቸው የምጣኔ ሀብት ባለሞያ የባንኮቹን ጤናማነት ከሚሰጡት አገልግሎትና ከደንበኞች እርካታ ጋር እያጣቀሱ የጤናማነታቸው እውነተኝነት ላይ ጥያቄ ያነሱበታል፡፡


ባለሞያው አቶ ያዕቆብ በቀለ የባንኮች የተቀማጭ መጨመር፤ ገንዘብ ከባንክ ውጪ እንደይሆን በመባሉ በግዴታም ጭምር ስለተደረገ መጨመሩን ተናግረዋል፡፡


‘’ብርን እንኳን በቀን ማውጣት የሚቻለው በገደብ ነው፣ ሰው ታሞ አንኳን 20 ሺህ ብር ስጡን ሲባሉ የማይሰጡ ብዙ ብንኮች አሉ’’ ሲሉ ይናገራሉ፡፡


ከኢትዮጵያ ሁሉም ባንኮች ብድር የወሰዱ ሰዎች ብዛት 350 ሺህ አካባቢ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡


ብሄራዊ ባንክ በቅርቡ ይፋ ባደረገው ሪፖርት ላይ እንደሰፈረውም የባንክ ብድሮች በጥቂት ተበዳሪዎች ጋር ተከማችቷል፡፡


ሪፖርቱ ላይ እንደተቀሰው ሁሉም ባንኮች እስከ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ድረስ ከሰጡት 1.9 ትሪሊዮን ብር ብድር ውስጥ 23.5 በመቶውን ያበደሩት ለአስር ተበዳሪዎ ብቻ ነው፡፡


ይህ እንዳለ ሆኖ አንዳንድ ባንኮች ደግሞ ለሀላፊዎቻቸው የሚሰጡትን ብድር ጤናማነት አቶ ያዕቆብ ይጠይቃሉ፡፡


ንጋቱ ሙሉ



Recent Posts

See All
ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።

ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው። አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው  ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page