top of page

ግንቦት 30፣2016 - አጠቃላይ ባንኮች የሰጡት ብድር ከ2 ትሪሊዮን ብር በላይ ደርሷል

  • Jun 7, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ ያሉት ባንኮች ትርፋማነታቸው፣ ያላቸው ሀብት፣ ካፒታል፣ የቁጠባ መጠን እና በሌሎች አሃዛዊ መረጃዎች እየተጠቀሱላቸው በጥሩ ጎዳና ላይ መሆናቸው ሲነገር ይሰማል፡፡


ለአብነትም የባንኮች ተቀማጭ ከ 2.29 ትሪሊዮን ብር በላይ ደርሷል፡፡


በዚህ ዓመት ስድስት ወራት ብቻ ከ 124.2 ቢሊየን ብር በላይ አዲስ ተቀማጭ ገንዘብ ባንኮቹ ሰብስበዋል፡፡


አጠቃላይ ባንኮች የሰጡት ብድርም ከሁለት ትሪሊዮን ብር በላይ ደርሷል፡፡


ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ ባወጣው እና የባንኮችን ሁኔታ በሚያስረዳው ሪፖርቱ የሀገሪቱ ባንኮች ከሚሰጡት ብድር አብዛኛው የተከማቸው በጥቂት ተበዳሪዎች ነው ማለቱ ይታወሳል፡፡


ሆኖም ግን ባንኩ የሀገሪቱ ባንኮች በአብዛኛዎቹ መለኪያዎች ጤናማ ናቸው ይላል፡፡


ሸገር ያነጋገራቸው የምጣኔ ሀብት ባለሞያ የባንኮቹን ጤናማነት ከሚሰጡት አገልግሎትና ከደንበኞች እርካታ ጋር እያጣቀሱ የጤናማነታቸው እውነተኝነት ላይ ጥያቄ ያነሱበታል፡፡


ባለሞያው አቶ ያዕቆብ በቀለ የባንኮች የተቀማጭ መጨመር፤ ገንዘብ ከባንክ ውጪ እንደይሆን በመባሉ በግዴታም ጭምር ስለተደረገ መጨመሩን ተናግረዋል፡፡


‘’ብርን እንኳን በቀን ማውጣት የሚቻለው በገደብ ነው፣ ሰው ታሞ አንኳን 20 ሺህ ብር ስጡን ሲባሉ የማይሰጡ ብዙ ብንኮች አሉ’’ ሲሉ ይናገራሉ፡፡


ከኢትዮጵያ ሁሉም ባንኮች ብድር የወሰዱ ሰዎች ብዛት 350 ሺህ አካባቢ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡


ብሄራዊ ባንክ በቅርቡ ይፋ ባደረገው ሪፖርት ላይ እንደሰፈረውም የባንክ ብድሮች በጥቂት ተበዳሪዎች ጋር ተከማችቷል፡፡


ሪፖርቱ ላይ እንደተቀሰው ሁሉም ባንኮች እስከ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ድረስ ከሰጡት 1.9 ትሪሊዮን ብር ብድር ውስጥ 23.5 በመቶውን ያበደሩት ለአስር ተበዳሪዎ ብቻ ነው፡፡


ይህ እንዳለ ሆኖ አንዳንድ ባንኮች ደግሞ ለሀላፊዎቻቸው የሚሰጡትን ብድር ጤናማነት አቶ ያዕቆብ ይጠይቃሉ፡፡


ንጋቱ ሙሉ



Recent Posts

See All
የነሐሴ 4 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሳውዲ_አረቢያ በሳውዲ አረቢያ ጂዛን በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ከባድ ቃጠሎ ተቅስቅሶ ነበር ተባለ፡፡ በጂዛኑ ማጣሪያ ላይ ቃጠሎ ተቅስቅሶ የነበረው ከባድ ፍንዳታ ከተሰማ በኋላ እንደሆነ አናዶሉ ፅፏል፡፡ በጁቢየል የተፈጥሮ ጋዝ ማሰናጃ ከተማም ቃጠሎ ተቀስቅሶ ነበር ተብሏል፡፡ የሳውዲ ምንጮች ቃጠሎዎቹ ተቀስቅሰው እ

 
 
 
በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡

ነሐሴ 4 2018 በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት በበኩሉ ሳያጠፋ የምንቀጣው አሽከርካሪ የለም እንዲያውም ሁሉንም ህጎች እናስከብር ብንል የማይቀጣ አሽከርካሪ አይኖርም ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.... ምህረት ስዩም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page