top of page

ግንቦት 26፣2016 - ምጣኔ ሐብት:- የዋጋ ግሽበት

  • Jun 3, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ ያለው የዋጋ ግሽበት፤ በከፍተኛነቱ ከአፍሪካ በ2ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል የሚል ሪፖርት ከወራት በፊት ይፉ መደረጉ ይታወሳል።


በአሁ ሰዓትም የሀገሪቱ የዋጋ ግሽበት 23 በመቶ እንደሆነ የገንዘብ ሚኒስቴር ተናግሯል።


ከሁለት አሃዝ ዝቅ አልል ብሎ፤ በተለይ የወር ደሞዝተኛውን እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ሰዎች ኑሮ ያከበደውን የዋጋ ግሽበት ለመቀነስ መንግስት ጥብቅ የሆነ የገንዘብ እና ፊስካል ፖሊሲ ማሻሻያዎችን አድርጌያለሁ ማለቱ ይታውሳል።


በዚህም፤ መንግስት ከብሔራዊ ባንክ የሚወስደው ቀጥተኛ ብድር አምና ከነበረው 147 ቢሊዮን ብር ዘንድሮ ወደ 57 ቢሊዮን ብር መውረዱን፣ የባንኮች የማበደር መጠን በ14 በመቶ እንዲገታ መደረጉን መንግስት ይጠቅሳል።

የስንዴ እና የሩዝ ምርት እንዲጨምር መደረጉን፣ የተማሪዎች ምገባ፣ ጎስቋላ የአቅመ ደካማ ቤት እንዲታደሱ ማድረጉን የዋጋ ግሽበቱ ለመቀነስ ከሰራቸው ስራዎች መካከል መሆኑን መንግስት ጨምሮ ያስረዳል።


መንግስት ይቅርብኝ ያለው፤ 17 ቢሊዮን ብር የፍራንኮ ቫሉታ ጉዳይም እዙሁ ጋ ይጠቀሳል።


ግን ግሽበቱ የማክሮ ኢኮኖሚ ራስ ምታት ሆኖ ቀጥሏል።


ንጋቱ ሙሉ



Recent Posts

See All
ዘንድሮ በአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች 66 በመቶዎቹ ተማሪዎቻቸው ሙሉ በሙሉ የማለፊያ ነጥብ አምጥተዋል፡፡

ሰኔ 22/2018 ዘንድሮ በአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች 66 በመቶዎቹ ተማሪዎቻቸው ሙሉ በሙሉ የማለፊያ ነጥብ አምጥተዋል፡፡ የከተማዋ ትምህርት ቢሮ በሰጠው መግለጫ ከመንግስት ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች 95 ነጥብ 8 በመቶ፤ ከግል ት/ቤት ተማሪዎች ደግሞ ከ99

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page