top of page

ግንቦት 22፣2016 - ማዕድን አሉባቸው የሚባሉ ቦታዎች አብዛኞቹ ታጣቂዎች የሚንቀሳቀሱባቸው ናቸው ተባለ

  • May 30, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ የማዕድን ሀብት አሉባቸው የሚባሉ ቦታዎች አብዛኞቹ ታጣቂዎች የሚንቀሳቀሱባቸው ናቸው ተባለ፡፡


ይህም የሀገሪቱ ማዕድን እንዳይለማ ችግር እንደሆነ ተነግሯል፡፡


የማዕድን ሀብት ባሉባችው የተለያዩ አካባቢዎች የሸመቁ ተዋጊዎችን ከቦታቸው ማስለቀቅ ከባድ ነውም ተብሏል፡፡


ከእነዚህ ቦታዎች መካከልም፤ አማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዋድላ ደላንታ፣ ኦሮሚያ ክልል ጉጂ፣ ጋምቤላ እና ቤኒሻንጉልጉሙዝ በምሳሌነት ተጠቅሰዋል፡፡


በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ የፀጥታ ችግሮች ሀገሪቱ ከማዕድን ሀብት ዘርፍ ማግኘት የሚገባትን እያሳጧት እንደሆነም የማዕድን ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኝ ተናግረዋል፡፡


ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቶችን ‘’እንደ ፀጋ ተቀብሎ ከመጠቀም ይልቅ የግጭት መንስኤ’’ ሆነው እንደቆዩ አስረድተዋል፡፡


የማዕድን ሀብት ባለባቸው የአፍሪካ ሀገራት ሐብቶቹ የግጭት መነሻ እንደሆኑ በምሳሌነት ያነሱት አንድ የምክር ቤት አባል በኢትዮጵያም እየታየ ያለው ተመሳሳይ እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡


በሌላ በኩል ወርቅን ጨምሮ ሌሎች ማዕድን የሚመረትባቸው አካባቢ ያሉ ማህበረሰቦች ማግኘት የሚገባቸውን ጥቅም እያገኙ አይደለም ተብሏል፡፡


ማዕድን ባለባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ነዋሪዎቸን ተጠቃሚ ለማድረግ በፈንድ መልክ፣ ለመሰረተ ልማት(ለውሃ፣ ለትምህርት ቤት፣ ለመንገድ.. ወዘተ) መገንቢያነት የሚሰጠው ገንዘብም ክልሎች ለሌላ ሲያውሉት እንደሚሰተዋልም የማዕድን ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኝ ተናግረዋል፡፡


በአሁኑ ሰዓት በክልሎች ብቻ ፈቃድ የተሰጣቸው ከ378 የማዕድን አውጪ ማህበራት በሀገሪቱ እንደሚገኙ ተነግሯል፡፡


ማንያዘዋል ጌታሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw


Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio


Website: https://www.shegerfm.com/


Recent Posts

See All
የነሐሴ 4 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሳውዲ_አረቢያ በሳውዲ አረቢያ ጂዛን በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ከባድ ቃጠሎ ተቅስቅሶ ነበር ተባለ፡፡ በጂዛኑ ማጣሪያ ላይ ቃጠሎ ተቅስቅሶ የነበረው ከባድ ፍንዳታ ከተሰማ በኋላ እንደሆነ አናዶሉ ፅፏል፡፡ በጁቢየል የተፈጥሮ ጋዝ ማሰናጃ ከተማም ቃጠሎ ተቀስቅሶ ነበር ተብሏል፡፡ የሳውዲ ምንጮች ቃጠሎዎቹ ተቀስቅሰው እ

 
 
 
በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡

ነሐሴ 4 2018 በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት በበኩሉ ሳያጠፋ የምንቀጣው አሽከርካሪ የለም እንዲያውም ሁሉንም ህጎች እናስከብር ብንል የማይቀጣ አሽከርካሪ አይኖርም ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.... ምህረት ስዩም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page