ግንቦት 21 2017 - በኢትዮጵያ በየዓመቱ በጡት ካንሰር ከሚያዙ ሴቶች ውስጥ አብዛኛዎቹ ዘግይተው ወደ ህክምና የሚሄዱ በመሆኑ ህይወታቸውን ያጣሉ ተባለ፡፡
- sheger1021fm
- 2 days ago
- 1 min read
በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች ቀዳሚ የሆነው #የጡት_ካንሰር የብዙ ሴቶች ፈተና ሆኗል፤ በገዳይነቱም ቀዳሚ ነው፡፡
ነገር ግን ቀድሞ ከታወቀ እና በጊዜ ከተደረሰበት ታክመው መዳን እንደሚቻል ከህመሙ ያገገሙና በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የካንሰር ቅድመ ጥንቃቄ ላይ የሚሰሩ ሴቶች ይመሰክራሉ፡፡
የጡት ካንሰር በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ህመም ዓይነቶች በቀዳሚነቱ የመጀመሪያ መሆኑን የሚናገሩት በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም የህክምና ኮሌጅ የካንሰር ስፔሻሊስት ሀኪም የሆኑት ዶክተር ሙሉጌታ ካሳሁን ናቸው፡፡
የካንሰር ህመም በሰውነት ላይ ከመሰራጨቱ በፊት የተለያዩ ደረጃዎች እንዳሉት የሚናገሩት ዶክተር ሙሉጌታ ህመሙ ቀድሞ ከተደረሰበት ግን መታከም የሚችል ቢሆንም አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ ሴቶች መታከም የማይችልበት ደረጃ ላይ ሲደርስ ነው ወደ ህክምና የሚመጡት ይላሉ፡፡

በተለይ በከተሞች ላይ ያለው ጤናማ ያልሆነ ያኗኗር ሥርዓት ለካንሰር መከሰት ምክንያት መሆኑን የሚናገሩት ዶክተር ሙሉጌታ ነገር ግን አብዛኛዎቹ የካንሰር ዓይነቶች ለመታከም ከዘገዩ በኋላ የሚታወቁ መሆናቸው ችግሩን አክብዶታል ይላሉ፡፡
በብዛት በከተሞች ላይ ለካንሰር መከሰት እንደ ምክንያት ከሆኑት ውስጥ በቂ የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ማጨስ፣ ቶሎ አለመውለድ፣ ጡት አለማጥባት ይጠቀሳሉ ተብሏል፡፡
የጡት ካንሰር በአብዛኛው በአርባ አመት የዕድሜ ክልል ውስጥ ባሉ ሴቶች ላይ የሚከሰት ቢሆንም አሁን እየተለወጠ ከመጣው የአኗኗር ስርዓት ጋር በተገናኘ ግን በ30 እና ከዚያ እድሜ በታች ባሉ ሴቶች ላይ እንደሚታይ ተነግሯል፡፡
በዓለም ላይ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች የጡት ካንሰር ቀዳሚ ሲሆን በኢትዮጲያ ሴቶችን ለሞት ከሚያበቁ ህመሞች የጡት ካንሰር አንዱ ነው፡፡
በሀገሪቱ በየአመቱ በጡት ካንሰር ከሚጠቁ ሴቶች ውስጥ ከ50 በመቶ በላይ የሚሆኑት ህመሙ ከተባባሰ በኋላ ወደ ህክምና የሚሄዱ በመሆኑ ህይወታቸውን እንደሚያጡ ሰምተናል፡፡
ምህረት ስዩም
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
We are responding to your questions because we thought you might be unsure. Yes, having fun with Sizzling Chhatarpur Escort s is very safe, and we protect your information. You see, any information you discuss with your girl will remain between you and her if you are spending time with her.