top of page

ግንቦት 20፣2016 - በሙስና የተመዘበረን ሀብት የሚያስመልስ ገለልተኛ ተቋም እንቋቋም የሚጠይቅ የፖሊሲ ረቂቅ እየተሰናዳ ነው ተባለ፡፡

  • sheger1021fm
  • May 28, 2024
  • 1 min read

በሙስና የተመዘበረን ሀብት የሚያስመልስ ገለልተኛ ተቋም እንቋቋም የሚጠይቅ የፖሊሲ እረቂቀው እየተሰናዳ ነው ተባለ፡፡


የፖሊሲ ረቂቁ ‘’የስነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ፖሊሲ’’ የሚሰኝ ነው ተብሏል፡፡


ረቂቅ ፖሊሲው ፀድቆ ወደስራ የሚገባ ከሆነ በፀረ ሙስና ትግል እስካሁን በሀገር ደረጃ ወጥቶ ተግባራዊ የሆነ የመጀመርያው የፀረሙ ሙስና ፖሊሲ ይሆናል ሲል የተናገረው የስነምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን ነው፡፡


ረቂቅ ፖሊሲው ምን ፋይዳ አለው ምን የተለየ ነገር አለው ያልናቸው በስነ ምግባርና ጸረሙስና ኮሚሽን የኮሚሽነር ፅህፈት ቤት አማካሪ መስፍን በላይነህ የፖሊሲ ረቂቁ የፀረሙስና ትግሉ በአንድ ተቋም ብቻ እንዳይሆን እና ለሁሉም የመንግስት መስሪያቤቶች እና የመንግስት የልማት ድርጅቶች ኃላፊነት የሚሰጥ ነው ብለዋል፡፡


በዚህም የመንግስት መስሪያቤቶች የሙስና መከላከልን ስራ እንደ መደበኛ የስራ አካላቸው እንዲያደርጉት የሚጠይቅ ነው ተብሏል፡፡


የመስርያ ቤቶችን አመታዊ የሙስና መከላከል ስራ የሚከታተልና ድጋፍ የሚያደርግ ምክር ቤት በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲቋቋምም ረቂቅ ፖሊሲው ይጠይቃል፡፡

ree

የስነምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን የውሸት ሪፖርትን እና በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚዘረፍን ሀብት ለመከላከል እንደሚረዳው ተናግሯል፡፡


ረቂቅ ፖሊሲው ሳይደረግ ተደረገ ሳይሰራ ተሰራ እየተባሉ የሚቀርቡ ሪፖርቶችን ለመከታተልና ለማረጋገጥ ይበጃል ተብሏል፡፡


በሙስና የተመዘበረን ሀብት በፊት የማስመለሱን ስራ ሲሰራ የነበረው የፍትህ ሚንስቴር ነው ያሉት አቶ መስፍን አሁን ግን የተሰናዳው ረቂቅ ለብቻው የተመዘበረን ሀብት የሚያስመልስ ገለልተኛ ተቋም እንዲቋቋም የሚጠይቅ ነው ብለዋል፡፡


ያሬድ አንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw


Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio


Website: https://www.shegerfm.com/


Recent Posts

See All
ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።

ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው። አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው  ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page