top of page

ግንቦት 15፣2016 - ትናንት ሌሊት እና ዛሬ ማለዳ በአዲስ አበባ ሁለት አደጋዎች ደርሰዋል

  • May 23, 2024
  • 1 min read

ትናንት ሌሊት እና ዛሬ ማለዳ በአዲስ አበባ ሁለት አደጋዎች ደርሰዋል፡፡


አንደኛው የእሳት ቃጠሎ ሲሆን ሌላኛው የአፈር መናድ አደጋ መሆኑን የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ተናግሯል፡፡


ዛሬ ማለዳ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው ተስፋዬ ወፍጮ ቤት አካባቢ በሚገነባ ህንፃ መሰረት ስር ብረት ሲያስሩ በነበሩ ሰራተኞች ላይ አፋፍ ላይ የነበረ የሌላ ቤት ውሃ ልክና አፈሩ ተደርሶባቸዋል ተብሏል፡፡


አደጋውን ተከትሎ ከናዳው ስር በአፈር የተቀበሩ ሰዎች አሉ የሚል ጥቆማ ደርሶት ኮሚሽኑ በስካቫተር የተናደውን አፈር በመቆፈር አንድ 28 አመት ወጣት አስከሬን ማውጣቱን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያው አቶ ንጋቱ ማሞ ለሸገር ተናግረዋል፡፡


ከሚገነባው ህንፃ አጠብ የነበረው የጭቃ ቤት አብዛኛው ተንዶ ቀሪው አየር ላይ ተንጠልጥሏል ብለዋል ባለሙያው፡፡


በሌላ በኩል ሌሊት 10 ሰዓት ላይ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 18 ማዞሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአንድ የፕላስቲክ ፋብሪካ ላይ የእሳት አደጋ አጋጥሞ የንብረት ውድመት መድረሱን አቶ ንጋቱ ነግረውናል፡፡


ማሽኖችን ጥሬ እቀዋዎችን ጨምሮ ፋብሪካው በከፊል ወድሟል የተባለ ሲሆን እሳቱ አቅራቢያው ወዳሉ መኖሪያ ቤቶች እና ድርጅቶች ላይ ተጨማሪ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር ውሏል ተብሏል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw


Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio


Website: https://www.shegerfm.com/


Recent Posts

See All
ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡

ሐምሌ 21 2018 ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡ የዓሣ ምርቱ ወደ መሃል ሃገር እየተጫነ ለአዲስ አበባ ገበያ እየቀረበ ነውም ተብሏል፡፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ መገንባቱን ተከትሎ በተፈጠረው ንጋት ሰው ሰራሽ ሃይቅ በኢትዮጵያ ትልቁና ከ70 በላይ ደሴቶች ያሉት የውሃ አካል ነው፡፡ ከቅርብ

 
 
 
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 30.65 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ የኃይል ማስፋፊያ ዕቅድ ይፋ አደረገ።

ሐምሌ 20 2018 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 30.65 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ የኃይል ማስፋፊያ ዕቅድ ይፋ አደረገ። እቅዱ የኔትወርክ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ፣ የሰብስቴሽን እና ተያያዥ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች፣ ስማርት ግሪድ እና ቆጣሪ ማስፋፋትን እንደሚያካትት አገልግሎቱ ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page