top of page

ግንቦት 13 2017 - ኢትዮጵያ በየጊዜው የሚወጡ የአደጋ መከላከል ቅድመ ትንበያዎችን ወደ ተግባር የመቀየር ችግር አለባት ተባለ

  • sheger1021fm
  • 8 minutes ago
  • 1 min read

ኢትዮጵያ በየጊዜው የሚወጡ የአደጋ መከላከል ቅድመ ትንበያዎችን ወደ ተግባር የመቀየር ችግር አለባት ተባለ፡፡


ይህ የሚሆነው የተግባር ስራው ብዙ ገንዘብ መመደብን የሚፈልግና ውድም ስለሆነ ነው ተብሏል፡፡


ይህን ያለው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ወይም ኢጋድ የአየር ጠባይ ትንበያ ትግበራ ማዕከል ነው፡፡


ኢትዮጵያ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የቅድመ አደጋ መከላከል ስራዎችን ሙሉ ለሙሉ እንዳትከውን አድርጓታል ተብሏል፡፡


የኢጋድ የአደጋ መከላከል ስራ አስኪያጅ አህመድ አምድይሁን(ዶ/ር) ኢትዮጵያን እና የኢጋድ አባል አገራትን የአየር ሁኔታ በተመለከተ በአመት ሶስት ጊዜ የትንበያ መረጃዎች እና ቅድመ አደጋ መከላከል ማስጠንቀቂያዎችን እናወጣለን ብለዋል፡፡


ይሁን እንጂ በኢኮኖሚ ዝቅ ያሉ አገራት በኢጋድ በኩል የሚወጡ የቅድመ አደጋ መከላከል ማስጠንቀቂያዎችን ከመተግበር አኳያ ክፍተት አለ ይላሉ፡፡


ኢትዮጵያም ያላት የበጀት አቅም ውስን በመሆኑ ቅድመ አደጋ መከላከል ስራዎችን በሚገባ እንዳትከውን አድርጓታል ሲሉ ተናግረዋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….


ፍቅሩ አምባቸው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…






Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page