ግንቦት 12 2017 - የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ምክንያታዊ ያልሆነ የመብራት መጥፋትን አልታገስም አለ፡፡
- sheger1021fm
- May 20
- 1 min read
የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰጭ መ/ቤቱ ተቆጣጣሪ የሆነው ይኸው ድርጅት የተዘረጋ መስመር ባለመጠገን እና በተለይ በአዲስ አበባ በዛፍ ምክንያት የሚቋረጠው መብራት 47 በመቶ የሚሸፍን ነው ብሏል፡፡
ይህንንም ችግር ለመፍታት ክረምት ከመግባቱ በፊት ለማስተካከል ወደ ስራ ገብቻለሁ ብሏል፡፡
የኢትዮዽያ ኢንቨሰትመንት ሆልዲንግስ በአገልግሎቱ ላይ ከፍተኛ መቆራረጥ እንዳይኖርና አገልግሎት ሰጭውም ያለምክንያት ደንበኞቹን ቅር እንዳያሰኝ የቁጥጥር ስራዬን አበርትቻለሁ ብሏል፡፡

ወሬውን የኢትዮዽያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ(ዶር) ለሸገር ነግረዋል።
የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰጭ መ/ቤቱ ተቆጣጣሪ የሆነው ይኸው ድርጅት ስለ መብራት መጥፋት ምክንያታዊ ያልሆነ ሰበብ አልፈልግም ብሏል።
በሰበብ አስባቡ መብራት በመቆራረጥ ደንበኞቹ ቅር እንዳይሰኙም ለኢትየኦዽያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት እቅድ ተነድፎለታል ተብሏል።
ይህንን ጥራት ያለው አገልግሎትም እንዲሰጥ መንገዱን የአኢትዮዽያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ያሳየዋል መባሉን ሰምተናል።
ተህቦ ንጉሴ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
📌 Linkedin : https://shorturl.at/21bFN












Comments