top of page

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተከፈለ ካፒታሉ 5 ቢሊዮን ብር  እንደደረሰ ተናገረ፡፡

  • sheger1021fm
  • 2 hours ago
  • 1 min read

ታህሳስ 3/2018


ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተከፈለ ካፒታሉ 5 ቢሊዮን ብር  እንደደረሰ ተናገረ፡፡


ይህም  ትልቅ ስኬት ነው ብሏል፡፡


በ2016 በጀት ዓመት የባንኩ የተከፈለ ካፒታል 2.4 ቢሊዮን ብር እንደነበር ያስታወሰው ባንኩ  በአንድ ዓመት ውስጥ የ102 በመቶ አድገት በማምጣት 5 በሊዮን ብር አንደደረሰ ተናግሯል፡፡


ባንኮች ካፒታላቸውን 5 ቢሊዮን ብር እንዲያደርሱ ብሔራዊ ባንክ ያስቀመጠውን መስፈርት ያስታወሰው ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ  ከጊዜ ገደቡ በፊት ማሳካት መቻሉ በባስለክሲዮኖቹ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ዘንደ ያለውን ተቀባይነት ከጊዜ ወደ ጊዜ አያደገ መመጣቱን ያሳያል ብሏል፡፡

ree

ይህ በመሳካቱ ባንኩ ከሎሎች ባንኮች ጋር መዋሃድ ሳይጠበቅበት እንዲቀጥል እንደሚያስችለው አና የመዋሃድም እቅድ አንደሌለው ተናግሯል፡፡


ይህ እንዲሳካም በተለይ ባለአክሲዮኞች ከፍተኛ አስተዋጾ ማድረጋቸው ተጠቅሷል፡፡


ግሎባል ባንክ ኢትዮጰየ በ2017 በጀት ዓመት ከ 5.56  ቢሊዮን  ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን በአመታዊ ሪፖርቱ ተናግሯል፡፡


ይህም ባለፈው ዓመት ከተመዘገበው  ጋር ሲነፃፀር የ37 በመቶ ጨማሪ ማሳየቱን ተጠቅሷል፡፡


የባንኩ ጠቅላላ ሃብት በበጀት ዓመቱ መጨረሻ  34.4  ቢሊዮን መድረሱ የተነገረ ሲሆን  ይህም ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ 42 በመቶ እድገት አሳይቷል ተብሏል፡፡


ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ  በ2017 በጀት ዓመት 7.53 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ ገንዘብ መሰብሰቡን በሪፖርቱ ጠቅሷል፡፡


የባንኩን አጠቃላይ ተቀማጭ 25.75  ቢሊዮን ብር በላይ ደርሷል ተብሏል፡፡


ባንኩ በበጀት ዓመቱ ከታክስ፣ ከመጠባበቂያ እና ሌሎች ተቀናሾች በፊት ከ 1.17 ቢሊዮን ብር አትርፌያለሁ ይህም ከቀዳሚው አመት ጋር ሲመሳከር የ33 በመቶ ብልጫ አለው ብሏል፡፡


የቅርንጫፎቹ ብዛት 237፣ የደንበኞቹ ቁጥር ደግሞ 1.8 ሚሊዮን መድረሳቸወንም አስረድቷል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

  

Recent Posts

See All
ታህሳስ 3/2018 የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ካለፈው ሃምሌ ወር ወዲህ እያደገ መጥቷል ተባለ።

ኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮች ከምታመርተው የኤሌክትሪክ ሃይል 90 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል እንደሆነ ተጠቅሷል። በዘንድሮው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት ኢትዮጵያ ከውሃ እና ከነፋስ ከ15,300 ጊጋዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨቷ ተነግሯል። በየወሩ በአማካይ 3,800 ጊጋዋት ሰአት የኤ

 
 
 
ታህሳስ 3/2018 ባለፉት 4 ወራት በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የሚገባ የኮንትሮባንድ እቃዎች ቁጥር መጨመሩን የገቢዎች ሚኒስቴር ተናገረ፡፡

የገቢዎች ሚኒስቴር ይሄን ያለው ዛሬ በሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ለፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ4 ወር የስራ ክንው ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡ ሪፖርቱን ያቀረቡት የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ ከገቢ ኮንትሮባንድ ከ8 ቢሊዮን ብር በላይ ፣ ከወጪ ኮንትሮባንድ ደግሞ 0.6 ቢሊየን ብር

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page