ግለሰቦች ዲጂታል መታወቂያቸውን ትክክለኛነቱ እና ደህንነቱ በተረጋገጠ መልኩ መጠቀም እንዲችሉ የሚያግዝ አገልግሎት ይፋ ተደረገ።
- sheger1021fm
- 10 minutes ago
- 1 min read
ህዳር 30 2018
ግለሰቦች ዲጂታል መታወቂያቸውን ትክክለኛነቱ እና ደህንነቱ በተረጋገጠ መልኩ መጠቀም እንዲችሉ የሚያግዝ አገልግሎት ይፋ ተደረገ።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ የደህንነት የዲጅታል ሰርተፍኬት አገልግሎት ስርዓት ተበጅቶለታል፡፡
በዚህም አገልግሎት በፋይዳ ፕሮግራም ስር ለዜጎች የሚሰጠው እያንዳንዱ ዲጂታል መታወቂያ ትክክለኛነት፣ ሊረጋገጥ የሚችል፤ እና ህጋዊ ተቀባይነት ያለው እንዲሆን ያስችላል ተብሏል።

ይፋ የተደረገው ዲጂታል ሰርተፍኬት አገልግሎት የሰዎችን የግል መረጃ የመመዝበር እና በሀሰተኛ ስም የሚወጡ መታወቂያዎችን ለመቆጣጠር፣ አመሳስሎ የመስራት የማጭበርበር እና የማንነት መረጃን አላግባብ መጠቀምን ለመከላከልም ይረዳል ተብሎለታል።
የፋይዳ መታወቂያን የጀርባ ክፍል ኪው አር ኮድ በቀላሉ በስልክ ስካን በማስደረግ አጠቃላይ የግለሰቡን ሙሉን መረጃ እና ትክክለኛነት እንዲሁም ህጋዊነቱን በቀላሉ የሚያሳይ የአሰራር ስርአት ነው።
በተጨማሪም መታወቂያውን የሰጠው አካል ማን እንደሆነም በግልፅ ያስረዳል ተብሏል።
ፍቅሩ አምባቸው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🟦Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1








