top of page

የፌደራል ግብር ከፋዮች በኮቴ ክፍያ፣ ነጋዴዎች ደግሞ በግብር ሰብሳቢዎች ስነ ምግባር ጉድለት መማረራቸው በፓርላማው ተነገረ፡፡

  • sheger1021fm
  • 13 minutes ago
  • 2 min read

ታህሳስ 3/2018

 

የፌደራል ግብር ከፋዮች በኮቴ ክፍያ፣ ነጋዴዎች ደግሞ በግብር ሰብሳቢዎች ስነ ምግባር ጉድለት መማረራቸው በፓርላማው ተነገረ፡፡

 

የገቢዎች ሚኒስቴር በበኩሉ የኬላ ጉዳይ ከፍተኛ አጀንዳ ሆኖ መቆየቱን፤ እስካሁን ግን መፈታት እንዳልተቻለ ተናግሯል፡፡

 

የኮቴ ክፍያና የገቢ ሰብሳቢ ሰራተኞች ስነ ምግባር ጉዳይ ለህዝብ ተወካዬዎች ምክር ቤት እና ሌሎች ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት ማቅረቡን የፕላን ፣ በጀት  እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተናግሮ፤ ለዚህም ማብራሪያ እንዲሰጠው የገቢዎች ሚኒስቴርን ጠይቋል፡፡

 

ቋሚ ኮሚቴው ይህን የጠየቀው ዛሬ ታህሳስ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የገቢዎችን ሚኒስቴርን የ4 ወራት የስራ ክንውን ሪፖርትን ባደመጠበት ወቅት ነው፡፡

 

የሪፖርቱን ማብቃት ተከትሎ የቋሚ ኮሚቴውን ሪፖርት በንባብ ያቀረቡት የገቢ ዘርፍ ንዑስ ሰብሳቢ አቶ ደበበ በክልሎች የማዘጋጃ ቤቶች ገቢ ስም ሀገር አቋራጭ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የተቋቋሙ ኬላዎች ለንግድ ስርዓቱ እንቅፋት መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

 

ህገ ወጥ ኬላዎች፤ ግብር ከፋዬች ምርትና ግብዓት በሚያጓጉዙበት ወቅት የኮቴ ክፍያ እና ሌሎች ስያሜዎችን በመስጠት አንዳንድ ጊዜ ተሸከርካሪው በያዘው ምርት መጠን በማባዛት እንዲከፍሉ መገደዳቸውን አስረድተዋል፡፡

 

ይህም ለተደራራቢ ግብር ስለዳረጋቸው ቅሬታችውን ለምክር ቤቱ እና ለሚመለከታቸው አካለት ማቅረባቸውን አስታውሰው፤ ለምን ችግሩን መፍታት እንዳልተቻለ አቶ ደበበ ጠይቀዋል፡፡

 

የገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ የኬላ ጉዳይ ከፍተኛ አጀንዳ ሆኖ መቆየቱን ጠቁመው፤ አስካሁን ግን  መፈታት እንዳልተቻለ አስረድተዋል፡፡

 

ree

የኮቴ ክፍያ የፌደራል ግብር ከፋዬችን ስራ እና ግብይት እንደሚረብሽ እንዲሁም ኢንቨስትመንትን እንደሚያቀጨጭ የተወያየንበት ጉዳይ ቢሆንም ችግሩን ማስቀረት አልተቻለም ሲሉ ተናግረዋል፡፡

 

የጭነት ተሽከርካሪዎች ለሚያገኙት የማዘጋጃ ቤት አገልግሎት በመነሻቸው እና መዳረሻቸው ላይ ብቻ እንዲከፍሉ ከስምምነት ቢደረስም ከህግ ውጭ በየከተሞች በጫኑበት ልክ እየተሰላ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ ብለዋል፡፡

 

የጉሙሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቃበታ በበኩላቸው ጉዳዩን የማያውቀው የስራ ሃላፊም ሆነ የመንግስት ተቋም እንደሌለ አስረድተው ችግሩን ለመፍታት ግን ፍላጎት የለም ሲሉ አብራርተዋል፡፡

 

ree

ሌላው ቋሚ ኮሚቴው ምላሽ የጠየቀበት ጉዳይ በገቢ ስብሳቢ ባለሙያዎች ስነ ምግባር ጉድለት መማረርን የተመለከተ ነው፡፡

 

ቋሚ ኮሚቴው ከሰራተኛው የስነ ምግባር ጉድለት ጋር በተያያዘ በተለይም በኦዲት፣ በክትትል እና በቁጥጥር ምክንያት ከፍተኛ ምሬት ከነጋዴዎች እንደሚነሳ አስታውሶ ችግሩን ለመፍታት ምን እየተሰራ እንዳለ ጠይቋል፡፡

 

የገቢዎች ሚኒስቴር በበኩሉ የስራተኞችን የስነ ምግባር ጉድለት ሊያስቀር እና ችግሩንም ለማቅለል የሚረዳ አዲስ የኦዲት መመርያ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መግባቱን ተናግሯል፡፡

 

በለፉት አራት ወራት ከ170 በላይ በለሙያዎች ላይ የስነ ምግባር እርምጃ እንደተወሰዳቸው የተናገሩት የገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስተር አይናለም ንጉሴ ከዚህ ውስጥ 10ሩ ከስራ ተባረዋል ብለዋል፡፡

 

ሚኒስትሯ ችግሩን ለማቃለል ከእጅ ንክኪ ነጻ የሆነ አሰራር መዘርጋት መጀመሩን አብራርተዋል፡፡

 

ያሬድ እንዳሻው

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


 

Recent Posts

See All
ታህሳስ 3/2018 የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ካለፈው ሃምሌ ወር ወዲህ እያደገ መጥቷል ተባለ።

ኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮች ከምታመርተው የኤሌክትሪክ ሃይል 90 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል እንደሆነ ተጠቅሷል። በዘንድሮው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት ኢትዮጵያ ከውሃ እና ከነፋስ ከ15,300 ጊጋዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨቷ ተነግሯል። በየወሩ በአማካይ 3,800 ጊጋዋት ሰአት የኤ

 
 
 
ታህሳስ 3/2018 ባለፉት 4 ወራት በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የሚገባ የኮንትሮባንድ እቃዎች ቁጥር መጨመሩን የገቢዎች ሚኒስቴር ተናገረ፡፡

የገቢዎች ሚኒስቴር ይሄን ያለው ዛሬ በሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ለፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ4 ወር የስራ ክንው ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡ ሪፖርቱን ያቀረቡት የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ ከገቢ ኮንትሮባንድ ከ8 ቢሊዮን ብር በላይ ፣ ከወጪ ኮንትሮባንድ ደግሞ 0.6 ቢሊየን ብር

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page