top of page

የካቲት 22፣2016 - በ128ኛው ዓመት የዓድዋ ድል ምክንያት ለተሸከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ፖሊስ ተናገረ

  • Mar 1, 2024
  • 1 min read

በነገው ዕለት የሚከበረውን 128ኛው ዓመት የዓድዋ ድል ምክንያት ለተሸከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ተናገረ፡፡


የድል በዓሉ በአዲስ አበባ ፒያሳ የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እንደሚከበር ተነግሯል፡፡

በዓሉ በሚከበር ዕለት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም እና አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ለተሽከርካሪ ዝግ የሞሆኑ መንገዶችን ፖሊስ አስረድቷል፡፡



• ከአፍንጮ በር ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን


• ከሰሜን ሆቴል ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን


• ከዮሃንስ ቤተ ክርስቲያን ወደ አቡነ ጴጥሮስ


• ከአራት መንታ ወደ ጅንአድ


• ከይርጋ ሃይሌ የገበያ ማዕከል ወደ አቡነ ጴጥሮስ


• ከሃብተ ጊዮርጊስ ድልድይ ወደ ሱማሌ ተራ


• ከሱማሌ ተራ ወደ ኤሊያና ሆቴል(ባንኮዲሮማ) መስቀለኛ


• ከተክለ ሃይማኖት አደባባይ ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ


• ከአገር አስተዳደር መብራት( ኢሚግሬሽን) ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ


• ከንግድ ማተሚያ ቤት ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ


• ከአሮጌው ቄራ ወደ ባንኮ ዲሮማ መብራት


• ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ደጎል አደባባይ


• ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን


• ከመቅደላ ሆቴል ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን


• ከቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ወደ ቴሌ እና ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ፊት ለፊት ወደሚገኘው አደባባይ የሚወስዱት መንገዶች ነገ የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ/ም ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ ተብሏል፡፡


በዓሉ በሚከበርበት ዙሪያ ከዋዜማው ከዛሬ የካቲት 22 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ በዓሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ከላይ በተጠቀሱት መንገዶች እና ፕሮግሙ በሚካሄድበት በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ዙሪያ ተሽከርካሪን ማሳደርም ሆነ ለአጭርም ሆነ ለረጀም ሰዓት አቁሞ መሄድ ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑንም ፖሊስ አሳስቧል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Recent Posts

See All
የቤት ገዢዎችን የመግዛት አቅም ለማበርታት እንዲያግዝ ፖሊሲ የተዘጋጀለት የሞርጌጅ ባንክ እንዲቋቋም ተጠየቀ።

ሚያዝያ 20/2018 የቤት ገዢዎችን የመግዛት አቅም ለማበርታት እንዲያግዝ ፖሊሲ የተዘጋጀለት የሞርጌጅ ባንክ እንዲቋቋም ተጠየቀ። በኢትዮጵያ ያለው የግለሰቦች ቤት የመግዛት አቅም ከጊዜ ጊዜ እየቀነሰ መምጣት፣የብርየመግዛት አቅም መዳከም የግለሰቦች ቤት የመግዛት አቅም አብሮ ተዳክሟል ይላሉ የሪል እስቴት

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page