top of page

የናፍታ ነዳጅ አቅርቦት መጠን ከመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በፊት ወደ ነበረበት እንዲመለስ መንግስት መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ተናገሩ።

  • 11 minutes ago
  • 1 min read

ሚያዝያ 21/2018


የናፍታ ነዳጅ አቅርቦት መጠን ከመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በፊት ወደ ነበረበት እንዲመለስ መንግስት መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ተናገሩ።

ሚኒስትሩ በሰጡት መግለጫ ፥ በአሁኑ ወቅት ያለውን የምርትና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ በማየት የናፍታ አቅርቦት ወደነበረበት እንዲመለስ መንግሥት ወስኗል ብለዋል።


በማደያዎች ይቀርብ የነበረው የናፍታ  አቅርቦት በቀን በግማሽ ቀንሶ  እንደነበር ይታወሳል።


በዚህም መሰረት በቀን ይቀርብ የነበረው ናፍታ 4 ነጥብ 5 ሚሊየን ሊትር እንዲሆን ተወስኖ ነበር።

አሁን ላይ ግን ከጦርነቱ በፊት ይቀርብ የነበረው በቀን 9 ሚሊየን ሊትር ናፍታ እንዲገባ መንግስት ወስኗል ብለዋል።


ለዚህም መንግሥት ተጨማሪ 20 ቢሊየን ብር በወር ለነዳጅ ድጎማ እንደሚያደርግ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ተናግረዋል።


ናፍታው ከጅቡቲ ወደ አዲስ አበባ መጓጓዝ ጀምሯል ያሉት ሚኒስትሩ፥አጠቃላይ የነዳጅ ድጎማው ከ300 ቢሊየን ብር መብለጡን ጠቁመዋል።


ቤንዚን እና የአውሮላን ነዳጅም ከጦርነቱ በፊት በነበረው መጠን እየቀረበ እንደሆነ ጠቅሰዋል።


ለአዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ ለክልሎች ደግሞ ከነገ ጀምሮ ከጅቡቲ ናፍታ የማጓጓዝ ሥራ እንደሚከናወን ሚኒስትሩ መናገራቸውን ከገንዘብ ሚኒስቴር የማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

Recent Posts

See All
የቤት ገዢዎችን የመግዛት አቅም ለማበርታት እንዲያግዝ ፖሊሲ የተዘጋጀለት የሞርጌጅ ባንክ እንዲቋቋም ተጠየቀ።

ሚያዝያ 20/2018 የቤት ገዢዎችን የመግዛት አቅም ለማበርታት እንዲያግዝ ፖሊሲ የተዘጋጀለት የሞርጌጅ ባንክ እንዲቋቋም ተጠየቀ። በኢትዮጵያ ያለው የግለሰቦች ቤት የመግዛት አቅም ከጊዜ ጊዜ እየቀነሰ መምጣት፣የብርየመግዛት አቅም መዳከም የግለሰቦች ቤት የመግዛት አቅም አብሮ ተዳክሟል ይላሉ የሪል እስቴት

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page