top of page

የካቲት 20፣2016 - ግሎባል ባንክ ከኢትዮጵያ የሰነድ ሙዓለ ነዋይ ገበያ የ50 ሚሊዮን ብር ድርሻ መግዛቱ ተሰማ

  • Feb 28, 2024
  • 1 min read

ግሎባል ባንክ ከኢትዮጵያ የሰነድ ሙዓለ ነዋይ ገበያ የ50 ሚሊዮን ብር ድርሻ መግዛቱ ተሰማ፡፡


ባንኩ ከዘመንና ሲንቄ ባንክ ቀጥሎ የ50 ሚሊዮን ድርሻ በመግዛት ሶስተኛው ባንክ ሆኗል፡፡


የካፒታል ገበያ በኢትዮጵያ ስራ መጀመሩን ተከትሎ የፋይናንስ ተቋሞች ከሰነድ ሙዓለ ነዋይ ገበያ ድርሻ መግዛታቸው በኢትዮጵያ የተጀመረውን የካፒታል ገበያ ወደፊት እያበረታው ነው ተብሏል፡፡


የኢትዮጵያ የሰነድ መዋዕለ ነዋይ ገበያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ጥላሁን እስማኤል ባንኮች ገበያውን እየተቀላቀሉ መሆኑ በጎ ተግባር ነው ብለዋል።

የግሎባል ባንክ ፕሬዘደንት ተስፋዬ ቦሩ ባንኩ ከኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ላይ የ 5 በመቶ አክስዮን በመግዛቱ ና በኢትዮዽያ የካፒታል ገበያ ሂደት ላይ መሳተፉን እውቅና ሰጥተዋል።


ከዚህ ቀደም ኢትዮ ቴሌኮም፣ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ፣ የኢትዮጵያ መድን ድርጅት እንዲሁም ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት መስራች አባል መሆን የሚያስችላቸውን የ25 በመቶ ድርሻ ከኢትዮጵያ የሰነድ መዋለ ነዋይ ገበያ ገዝተዋል፡፡


ወሬውን የኢትዮጵያ የሰነዶች ሙዓለ ንዋይ ገበያ ለሸገር ነግሯል፡፡


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Recent Posts

See All
አስተማማኝ የጤና ሥርዓት ለመገንባት በሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርትን ማጠናከርና የፀረ-ተሕዋስያን መድኃኒቶችን አጠቃቀም ቁጥጥር ማጠናከር እንዲሁም የፋርማሲ ዘርፍ ጥናትና ምርምር ማሳደግ ያስፈልጋል ተባለ።

ሐምሌ 22 2018 አስተማማኝ የጤና ሥርዓት ለመገንባት በሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርትን ማጠናከርና የፀረ-ተሕዋስያን መድኃኒቶችን አጠቃቀም ቁጥጥር ማጠናከር እንዲሁም የፋርማሲ ዘርፍ ጥናትና ምርምር ማሳደግ ያስፈልጋል ተባለ። አስተማማኝ የጤና ሥርዓት ለመገንባት ኢትዮጵያ በመድኃኒት ምርት ራሷን መቻል እንዳለባት፣ በተ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page