top of page

የኢትዮጵያ ግብርና ለባለመዋዕለ ነዋዮች ሳቢ ያልሆነው ለምንድነው?

  • 2 hours ago
  • 1 min read

የካቲት 16/2018


ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ቢሆንም ሀብት እውቀታቸው ይዘው ወደዘረፋ የሚቀላቀሉ ባለመዋዕለ ነዋዮች ግን እንደሚፈለገው አይደለም፡፡


ባለሀብቶች ፣ ትራክተር እና ኮምፓልነር ይዘው ግብርና ከመስራት ይልቅ በሪል ስቴት ፣ በሆቴል በመሳሰሉትና በከተማ በሚሰሩ ዘርፎች በስፋት ሲሰማሩ ይታያል፡፡


የኢትዮጵያ ግብርና ለባለመዋዕለ ነዋዮች ሳቢ ያልሆነው ለምንድነው?


በሰብል እና ጥጥ የግብርና ዘርፍ ላይ ትሰማርተው የሚሰሩ ባለመዋዕለ ነዋዮች የፋይናንስ ፣ የመሰረተ ልማት አለመሟላት፣ የብድር አቅርቦት አለመመቻቸት ፣ የፀጥታ ችግር እና መሰል ችግሮች በእርሻው ልማት ላይ እየፈተናቸው መሆኑን ያስረዳሉ።


የግብርና ሚኒስቴር አልሚዎቹ ያነሷቸው ችግሮች መኖራቸውን ያምናል።



የግብርና ሚኒስቴርና ኢንቨስትመንትና ምርት ግብይት ዴስክ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ገብረስላሴ ባለመዋዕለ ነዋዮች ሀብታቸውን ፈሰስ አድርገው በእርሻ ልማቱ በበቂ ሁኔታ እንዳይሳተፉ እንቅፋት ናቸው ካሏቸው ጉዳዮች መካከል በቂ የግብርና ኢንሹራንስ አለመኖር ተጠቃሽ ነው።


ይህንን ችግር ለመፍታትም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በዘርፉ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የኢንሹራንስ ቁጥሩን ከፍ የማድረግ ፥ ብድር እንዲመቻችላቸውም ከአበዳሪ ተቋማት ጋር አብሮ የመስራት እንቅስቃሴዎችም አሉ ብለዋል ።


አቶ አለማየሁ ባለሃብቶች በግብርና ዘርፍ ተሰማርተው የእርሻ ልማቱ ላይ እንዳይሰሩ በርካታ ችግሮችን የጠቀሱልን ቢሆንም በእርሻ ልማት የሚሳተፉ አልሚዎች ግን ከባለፉት ዓመታት አንጻር ቁጥራቸው ከፍ እንዳለ ያነሳሉ ።


መሻሻም መጥቷል ፥ ይኸም የሆነው በዘርፉ የነበሩ ችግሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ በመቃለላቸው ነውም ይላሉ።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ……


ፍቅሩ አምባቸው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page