የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የገቢና ወጭ ጭነት ፍላጎት በብርቱ መጨመሩን እና ስራ እንደበዛበት ተናግሯል።
- 6 hours ago
- 1 min read
ሚያዝያ 1/2018

የ ኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የገቢና ወጭ ጭነት ፍላጎት በብርቱ መጨመሩን እና ስራ እንደበዛበት ተናግሯል።
በተለይ የመንግስት እና የግል ከፍተኛ ጭነቶች ከተፈጠረው ነዳጅ እጥረት ጋር በተገናኘ ሎጅስቲክሱ ፊቱን ወደ ባቡር አዙሯል ተብሏል።
ድርጅቱ ፤ ያሉትን ማጓጓዣዎች ጠባያቸውን እየቀየረ እና ከ ጉምሩክ ኮሚሽን ፈቃድ እየጠየቀ የምርመራ ቦታዎች በመዳረሻቸው እንዲሆኑ ጠይቋል።
ለዚህም ይረዳው ዘንድ የ ጎንዶላ ዋገኖችን መጠቀም መጀመሩን ሰምተናል።
ጎንዶላ ዋገን በጠባዩ የላይኛው ክፍሉ ክፍት ነው ፤ ይህም አይነት ዋገን በቀይ በቢጫ እና በአረንጔዴ የሚያልፋ ጭነቶች ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር መናበብን የሚጠይቅ እንደሆነ ይታወቃል።
ተህቦ ንጉሴ




Comments