የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለተጠቃሚዎች እራሱ ስጋ ለማቅረብ ሚያስችለውን ጥናት እያደረገ መሆኑን ተናገረ፡፡
- sheger1021fm
- 1 day ago
- 1 min read
ታህሳስ 30/2018
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለተጠቃሚዎች እራሱ ስጋ ለማቅረብ ሚያስችለውን ጥናት እያደረገ መሆኑን ተናገረ፡፡
ድርጅቱ ለገና በዓል 5,164 የቁም እንስሳት እርድ መፈፀሙን ነግሮናል፡፡
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አታክልቲ ገብረሚካኤል አስካሁን ድረስ ከደንበኞች ከበዓል እርድ ጋር በተያያዘ ቅሬታ እንዳልቀረበ ይናገራሉ፡፡
ከበዓሉ ቀደም ባለው ጊዜ ድርጁቱ በቂ ዝግጅት አድርጎ ነበር ያሉት አቶ አታክልቲ ስጋውን ለደንበኞች ለማቅረብ የሚገለገሉባቸው መኪኖችንም እንቅስቃሴ በካሜራ እና በጂፒኤስ ሲከታተሉ እንደነበር ያስረዳሉ፡፡

የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳር ፕሮጀክቶች ህገወጥ የቁም እንስሳት እርድ ከተማ ውስጥ እንዲቀንስ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው በሌላ በኩል ደግሞ አንዳንዶች ወደ ሸገር ከተማ በመሄድ ህገወጥ የእንስሳት እርድ ይፈፅማሉ ብለዋል አቶ አታክልቲ ገብረሚካኤል፡፡
ችግሩን ለመፍታት ከዚህ ቀደም ከሸገር ከተማ አስተዳደር ጋር ክፍተቶች ነበር አሁን ግን አብረን መስራት ጀምረናል ይላሉ፡፡
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አሁን እየሰራ ካለው ስራ በተጨማሪ ስጋን ለተጠቃሚዎች እራሱ ለማቅረብ የሚያስችለው አሰራር ለመዘርጋት ጥናት እያደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አታክልቲ ገብረሚካኤል ተናግረዋል፡፡
ጥናቱ ተጠናቆ በሚቀመጠው መፍትሄ በመነሳት ቄራዎች ድርጅት ሉካንዳቤቶት አገልግሎት ይሰጣል ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አሁን ላይ የቁም እንስሳት እርድን አገልግሎት እየሰጠሁ ነው ያለ ሲሆን የስጋ ተረፈምርቶችን ለሀገር ውስጥና ለውጪ ገብያዎች እያቀረበ መሆኑን አቶ አታክልቲ ጠቅሰዋል፡፡
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1











Comments