የአካቶ ትምህርት ስርዓት ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች
- 8 minutes ago
- 1 min read
መጋቢት 25/2018
በአካቶ ትምህርት ስርዓት አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች እንዳለባቸው ችግር ተለይተው እንደማንኛውም ሰው የትምህርት እድል እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ቢባልም ልዩ ፍላጎት የሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች ግን ጎዶሎዎች እንዳሉባቸው ይናገራሉ፡፡
በልዩ ፍላጎት የሰለጠነ በቂ መምህራን አለመኖር፣ የትምህርት ቁሳቁስ እጥረት፣ የመሰረተ ልማት ምቹ አለመሆንን ጨምሮ ሌሎች ችግሮች እንዳሉባቸው ያነሳሉ፡፡
ትምህርት ሚኒስቴርም በበኩሉ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የሚያነሱት ቅሬታ ትክክል ነው ለዚህ ደግሞ እንደ እኩዮቻቸው የትምህርት እድል እንዲያገኙ የአካቶ ትምህርት ሥርዓትን ዘርግቼ እየሰራሁ ነው ብሏል፡፡
በተለይ የአካቶ ትምህርት ትግበራ ሲታሰብ የቁሳቁስ እጥረት፣ የሰለጠኑ መምህራን አለመኖር፣ የመሰረተ ልማት ምቹ አለመሆን በዋናነት የሚነሱ ጥያቄዎች ናቸው ያለው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እነዚህን ችግሮች በሙሉ ለመሙላት የሚያስችል በቂ የገንዘብ አቅም የለኝም ብሏል፡፡
ተማሪዎቹ ያሉባቸውን ችግሮች በአንዴ መሙላት ባልችል እንኳን የተወሰኑ ትምህርት ቤቶችን እየመረጥኩ የሚያስፈልጓቸውን ቁሳቁስ እያሟላሁ ነው ሲል ነግሮናል፡፡
የሚመረጡት ትምህርት ቤቶችም ላይ በቂ ገንዘብ እንደሚመደብ ያነሳው መስሪያ ቤቱ የትምህርት ቁሳቁስ ማሟላት፣ ትምህርት ቤቱ ለተማሪዎቹ ምቹ እንዲሆን አድርጎ መገንባትን ጨምሮ ሌሎች ስራዎች ይከወንባቸዋል ብሏል፡፡
ነገር ግን አጠቃላይ በኢትዮጵያ ባሉ ትምህርት ቤቶች ላይ እንዲህ ዓይነት ስራዎችን ለመስራት የገንዘብ እጥረት ስለሚጋጥም የተወሰኑ ትምህርት ቤቶችን በመምረጥ የአካቶ ትምህርት ድጋፍ መስጫ ማዕከል እንዲሆኑ እየተደረገ ነው መባሉን ሰምተናል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
ፋሲካ ሙሉወርቅ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments