top of page

የተፈጠረውን የነዳጅ እጥረት ተከትሎ የጭነት መኪኖች ምልልስ በመቀነሱ የወጪ ንግዱ የሚላክበት ኮንቴይነር እጥረት ማጋጠሙ ተሰምቷል፡፡

  • 1 hour ago
  • 1 min read

መጋቢት 25/2018


በሀገር ውስጥ የተፈጠረውን የነዳጅ እጥረት ተከትሎ የጭነት መኪኖች ምልልስ በመቀነሱ የወጪ ንግዱ የሚላክበት ኮንቴይነር እጥረት ማጋጠሙ ተሰምቷል፡፡


በጅቡቲ የባዶ ኮንቴይነሮች ክምችት ቢጨምርም መኪኖች ወደ ሀገር ቤት በበቂ ሁኔታ ሊያመጧቸው ስላልቻሉ የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ድርጅት ባዶ ኮንቴነሮችን ወደ ሀገር እያስገባ እንደሚገኝ ነግሮናል።


የኢትዮ ጁቡቲ ምድር ባቡር ድርጅት የቢዝነስ ደቨሎፕመንት እና የማርኬቲንግ ክፍል ሃላፊ ኤደን ተስፋዬ በተለይ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ለተሰማሩ ድርጅቶች ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።


ላኪዎች ከድርጅቱ ጋር እንዲሰሩ እና በተፈጠረው ችግር ምክንያት መስተጓጎል እንዳይኖር እንዳያደርጉም ሃላፊዋ ጥሪ አቅርበዋል።


ድርጅቱ ለወጪ ንግዱ ቅድሚያ በመስጠት ጭነቶችን ለማመላለስ ዝግጅት እንደጨረሰም ተሰምቷል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….



ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page