የህክምና አገልግሎትን ያሻሽላሉ የተባሉ ቴክኖሎጂዎችን የሚያቀርቡ 8 ሀገራት ተቋሞቻቸውን የሚያሳትፉበት ዓለም አቀፍ ጉባኤ ሊካሄድ ነው።
- 3 hours ago
- 1 min read
መጋቢት 9/2018
የህክምናውን ዘርፍ ያሳድጋሉ፣ የህክምና አገልግሎትን ያሻሽላሉ የተባሉ ቴክኖሎጂዎችን እና መፍትሄዎችን የሚያቀርቡ ከተለያዩ 8 ሀገራት ተቋሞቻቸውን የሚያሳትፉበት ዓለም አቀፍ ጉባኤ ሊካሄድ ነው።
ከ10ኛው ኢትዮ ኸልዝ ጉባኤ ጎን ለጎን 2ኛው የሀገር ውስጥ የህክምና ግብዓት ምርትና ፈጠራዎች ኤግዚቢሽን ከመጋቢት 24 እስከ 26/2018 ዓ.ም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር ይካሄዳል ተብሏል።
ኤግዚቢሽኑ የሀገር ውስጥ የህክምና መሣሪያዎች፣ የመድኃኒት አምራቾች እና የጤና ቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን ለማበረታታትና ለገበያ ለማቅረብ የሚረዳ መሆኑም ተነግሯል።
በተጨማሪም የሀገር ውስጥ አምራቾች ከዓለም አቀፍ አምራቾች ጋር እንዲተሳሰሩ፣ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎቻቸውን እንዲያስተዋውቁ እና በዘርፉ ካሉ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የንግድ ተስስር እንዲፈጠር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ተብሎለታል።
ኤግዚቢሽኑን ጤና ሚኒስቴር፣ አርማወር ሀንሰን የምርምር ኢኒስቲትዩት እና ፕራና ኢቨንትስ በጋራ እንደሚያዘጋጁትም ሰምተናል።
ከ8 የአለም ሀገራት የተውጣጡ ከ90 በላይ ኩባንያዎች እንደሚሳተፉም ተነግሯል።
ሁነቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እና አቅራቢዎችን በማስተዋወቅ፣ የቴክኖሎጂ እና የዕውቀት ሽግግርን በማምጣት ለዘርፉ ልማት በሚደረገው ጥረት ቁልፍ ሚና እንደሚኖረውም ታምኖበታል።
በተጨማሪም ከ40 በላይ የሞያ ማጎልበቻ (CPD) ስልጠናዎች፣ 3ኛው የዲጂታል ኸልዝ እና ሳይንሳዊ ፎረሞች የኹነቱ አካል ናቸው ተብሏል።
ባንግላዲሽ፡ ቻይና፣ ህንድ፣ ሩሲያ፣ ቱርክ፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ፣ አሜሪካ እና አዘጋጇ ኢትዮጵያን ጨምሮ የጉባኤው ተሳታፊዎች ይሆናሉ ተብሏል፡፡
ፍቅሩ አምባቸው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments